በጎንደሩ ግጭት የበርካታ ሰው ህይወት ጠፋ

ትናንት በጎንደር ከተማ በተቀሰቀሰ ግጭት በሰዎች ህይወት፣ አካል ጉዳትና ንብረት ውድመት ምክንያት የሆኑ አካላት ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ እንደሚወስድ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ፡፡ በግጭቱ የሞቱና የተገዱ ሰዎችን አጣርቶ ይፋ እንደሚደርግም የክልሉ መንግሥት ትናንት ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር በበኩሉ በግጭቱ የእስልምና እና የክርስትና ዕምነት ተከታይ የሆኑ የከተማይቱ ነዋሪዎች መገደላቸውን አመልክቷል፡፡ በሌላ በኩል በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ቤተ እምነቶች ባስተላላፉት ጥሪ “መንግሥት ለንጹሃን ሞት ምክንያት የሆኑ ህገ ወጥ ተግባራትን ያስቁም” ብለዋል። “‘.. ማንም ይሁኑ ማን ድርጊቱን የፈጸሙ ወገኖችንም ተጠያቂ እንዲያደርግ” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተሰረዘው የነቢዚ ሲግናል፣ ጃሉድና ናቲማን ኮንሰርት ከ2 ሳምንት በኋላ ይደረጋል ተባለ

Leave a Reply

Your email address will not be published.