አማራው የሚዘምተው በታማኝ የቁርጥ ቀን የእማራ ልጆች አመራር ስር ብቻ ሆኖ ነው (እውነቱ ቢሆን)

የአውሬውና ተንኮለኛው የአብይ አህመድ አገዛዝ ጀግናውን ፋኖን ኢመደበኛ ብሎ ገሚሱን አሰሮ ገሚሱን ደግሞ ጥቁር ክላሽ ዘርፏል ብሎ እያሳደደ ባለበት ሁኔታ ውስጥ አሁን አብይ ራሱ ከወያኔ ጋር ተናብቦ  በጸረአማራነት ሴራ በጋራ አሲረው ሁለቱ ላስጀመሩት ጦርነት ፋኖን፣ የአማራ ወጣትን የአማራ ህዝብን ምስለኔወቹ “ ”ና ዝመት” ” እያሉ ጥሪ እያካሄዱለት ነው፡፡ የፌደራል መንግስት ተብየውም እንደዚሁ ጥሪ እያካሄደ ነው፡፡

የአማራ ዘማች ሆይ፦ አንተ ከመሀል ስትገባ ከወዲያ ወያኔ ከወዲህ ኦሮሙማ ሆኖ ጭዳ ሊያድርጉህ ያሰቡትን ቅዠታቸውን ንቃበት፡  በዚህ መልኩ አማራ ይሰልፋል ማለት መቃዠት መሆኑን ለሁለቱም ጠላቶችህ  ንገራቸውና በራስህ ተደራጅተህ በሁለቱም ላይ በራስህ ጊዜ፣ በራስህ ፕላን፣ በራስህ አመራር ዝመት፡፡  አንድ የማይካድ ሀቅ አለ፡፡  ወያኔ አንደኛ ደረጃ የአማራ ጠላት ስለሆነ ሊዘመትበት ግድ ይላል፡፡አማራው ወያኔን ድል ማድረግና ማጥፋት አማራ ለሆነ ሁሉ የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ ነው፡፡  ምክንያቱም አማራን ደጋግመው ክደውታል፡፡  ምሳሌ በበፊቱ ወረራ ደሴ ላይ በአሁኑ ወረራ ደግሞ ቆቦ ላይ ይህንኑ በተግባር ፈጽመውታል፡፡  ምክንያቱም አማራን ጠላታችን ነው ብለው በወያኔ ማኒፊስቶ ላይ አስፍረውታል፡፡ ምክንያቱም  ህዝቡን አማራ ጠላትህ ነው ብለው ለዘመናት ሰብከውታል፡፡ ስለዚህ ወያኔ (የትግራይ ህዝብ አላልንም) የአማራ አንደኛ ደረጃ ጠላት ስለሆነ መጥፋት አለበት፡፡   ስለዚህም ነው አማራ በወያኔ ላይ የሚዘምተው፡፡

አማራ በኦሮሙማ ላይም ይዘምታል፡፡የኦሮሙማ ክፍልፋዮች አንድ የሚስማሙበት ጉዳይ አለ፡፡ እርሱም ወሎ (ሰሜን ኦሞም ነው የሚለው ከንቱ ትርክታቸው ነው፡፡ ስለሆነም ኦሮሙማም የአማራ ጠላት ነውና አማራው ኦሮሙማ እስካልታረመ  ድረስ ይዘምትበታል፡፡  በወለጋ በቅርቡ በየቀኑ አንድ ሽህ አማራወችን እያረደ ግዳይ ይጥል የነበረው በአብይ አህመድ አገዛዝ በእጅ አዙር የሚደገፈው በዳቦ ስሙ ሸኔ እያሉ የሚጠሩት የኦሮሙማ ቡድን መሆኑን ሁሉም ያውቃል፡፡ ማን ሆነና ነው ሰው ገድሎ ዘቅዝቆ የሰቀለው?? ማን ሆነና ነው እርጉዝ የአማራ ሴትን አርዶ ጥሎና  ሽሉን ከሆዷ ቀድዶ አውጥቶ ልጇን በእጇ ያስታቀፈው?? ይህ ይረሳልን??? ስለዚህ ከኦሮሙማ ጋር አማራው የሚያወራርደው ሂሳብ አለው፡፡  ይህ ጉዳይ ሽህ አመታት ቢወስድም ከአማራ ህሊና አይፋቅም፡፡ የሚብላላ የማይታጠፍ  የየትውልዱ የአማራነት  ምህላ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሮመዳን ዋዜማ እና ሮመዳን በሳውዲ አረቢያ! - ከነብዩ ሲራክ

በተለይ አሁን ላይ አማራ የሚዘምተው ባስገደሉት፣ ባሳሰሩት፣ አንገቱን ባስደፉት አሁን ባሉት ሹመኞች ማለትም የአማራ ብልጽግና ተብየወች ስር ሆኖ አይደለም፡  በእነርሱ አዝማችነት ስር ሆኖ የሚዘምት አማራ የለም፡፡ ካለም ሞኝ፣ ሞኛ-ሞኝ፣ ጅል፣ ጅላጅልና ጅላንፎ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡  አሁን ላይ ዘግይቶም ቢሆን አማራ የጠላቶቹ የወያኔና የኦሮሙማ ስሌት ገብቶታል፡፤ ያልገባው ወይንም እንዳልገባው የሚያስመስለው ክፍል ቢኖር ሆዳሙና ጥቅመኛው ምስለኔው ብቻ ነው፡፡

እንድገምላችሁ፡፡ አማራው ይዘምታል፡፡ የሚዘምተው ግን በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ አመራር ስር ሆኖ ነው፡፡ የሚዘምተው ግን በእውቆቹና ጀግኖቹ የፋኖ መሪወች ስር ሆኖ ነው፡፡ በእነ ዘመነ ካሴ ፣ በእነ መሬ ወዳጆ፣  በእነ ጀኔራል ሀስን ከሪሞና …..ወዘተ ታማኝ የቁርጥ ቀን የእማራ ልጆች አመራር ስር ብቻ ሆኖ ነው፡፡ እነዚህ የቁርጥ ቀን የአማራ አርበኞች ደግሞ በአብይ አህመድ ትእዛዝ አብዛኛወቹ ታስረዋል፣ ተሰደዋል፡፡

መንግስት ተብየው የጅላንፎወች ስብስብ አሁን አገሪቱ ላለችበት አሳሳቢ የወረራ ድራማ  (ድራማው ቲያትር ካልሆነ) እነዚህ የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች በጦርነቱ ውስጥ ገንቢ ሚና ይጫወቱ ዘንድ ከፈለገ በይፋ በህዝብ ፊት በፋኖ ላይ ስህተት መስራቱን አምኖ ፋኖወችን ይቅርታ ሊጠይቃቸውና ዋስትና ሊሰጣቸውም ይገባል፡፡  (ነገሩ ስህተት ሳይሆን ተንኮል ነበር)፡፡ መንግስት ተብየው የጅላንፎወች ስብስብ በአለምና በኢትዮጵያ ህዝብ  ፊት ይህንን በይፋ ካደረገ  የተወሰነ ተአማኒነትን በስንዝርም ቢሆን  ሊያገኝ ስለሚችል ለራሱም ይጠቅመዋል፡፡ መንግስት ተብየው የጅላንፎወች ስብስብ ይህንን ካደረገ አማራው ነቅሎ ወጥቶና በራሱ ልጆች አዝማችነት ስር ብቻ ዘምቶ ወያኔን ድባቅ መትቶ በቀላሉ  ሊያሸንፋትና ከመሰረቷም ነቅሎ ሊጥላት አቅምና ወኔ ያለው ሀይል ነው፡፡ መንግስት ተብየው ስብስብ ይህ እንድሆን ካላደረገ አማራውም በአስገዳዮቹ ስር ይዘምታል ብሎ ማሰቡ ሞኝነት ነው የሚሆነው፡፡

እቅጩን እንናገር፡፡ አማራው በአብይ አህመድ አሽከሮች ማለትም ፣ ደመቀ መኮንን፣ ግርማ የሽጥላ  ዶ/ር ይበልጣል ከፋለና ወዘተ ለኦሮሙማው አገዛዝ ታማኝ በሆኑትና በተሸጡት የአማራ ሆዳም አመራሮች ስር ሆኖ አይዘምትም፡፤ በራሱ በፋኖወችና በራሱ የጎበዝ አለቆች አመራር ስር ብቻ ሆኖ ነው የሚዘምተው፡፤  መንግስት ተብየው የጅላንፎወች ስብስብስ በይፋ ወጥቶ ፋኖን ይቅርታ ጠይቆ ወደዘመቻው ካልሳበው ከሁሉ በፊት የአማራ ዘማች አፈሙዙን በብአደን ላይ ይደቅናል፡፡ ፋኖና ሌላው የማራ ህዝባዊ ሀይል ዘማች በቅድሚያ ይህን ካከናወነ በኋላ ለፋኖና ለአማራው ተዋጊ ሀይል ሌላው ጉዳይ ሁሉ እዳው ገብስ ነው የሚሆንለት፡፤ የወያኔም የኦሮሙማም እዳ ለሀያሉ የአማራ ክንድ ምኑም አይደለችም፡፤ የአማራው ዋናው ጠላቱ ሆዳም አማራወቹ ናቸው፡፡ እነዚህ ትርፍ አንጀቶች ወይ ይህንኑ አውቀው ከመንገዱ ገለል ይበሉለት፡፡ አለበለዚያም ራሱ እስከወዲያኛው ገለል ያደርጋቸዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሞትንማ ቆይተናል!!! -    ማላጂ

ለመድገም ያህል ወያኔ ወጥታ ወርዳ ልትይዝ የምትፈልገው ራያንና ወልቃይትን ሲሆን እነዚህን ታሪካዊ የአማራ ርስቶች ከአውሬው አብይ አህመድ ጋር ሴራ ጎነጎነችም ወይንም ከምእራባዊያን ጋር ዱሮ  ዘረፈችው ዶላር “”ፍጥምጥም”” ፈጸመች   ያ ቢወጣ ይህ ቢወርድ መቼም ቢሆን መቼም ራያንና ወልቃይትን መያዝና የወያኔ ርስት ማድረግ አይሳካላትም፡፤ ኦሮሙማም እንደዚሁ ወሎን ሰሜን ኦሮሚያ ነው  የሚለው ቅዠቱ ምንጊዜም አይሳካለትም፡፤ በጥቅሉ ሁሉም ይህንን አውቆ ካልተረዳና ካልታረመ በስተቀር በአገሪቱ ላይ የሚኖረው ተያይዞ እልቂት እንጅ ለአንዱ የተለየ ድል አይሆንለትም፡፡

ለማንም ቢሆን የፈለገውን ጊዜ ይወስዳል እንጅ ከሀቅና ከእውነት ውጭ የሚመጣ ቋሚ መፍትሄ አይኖርም፡፡ እልቂቱ ለሁሉም እልቂት ሆኖ ይቀጥላታል እንጅ የአማራውና የአፋሩ እልቂት ብቻ ሆኖ አይቀርም፡፡ መፍትሄው አንድና አንድ ነው፡፤ በሀቅና በታሪክ ላይ የተመሰረተ እውነት ብቻ፡፡

 

2 Comments

  1. ከጥቂት ወራቶች በፊት ወያኔ 60 ሽህ አባላቱን መርጦ አስቀድሞ በስደተኛ መልክ ወደ አማራ ክልል ወደ ቆቦ ከተማ ሲልካቸው የአማራ ምስለኔወች ይህንኑ አምነውም ሆነ የድራማው አጃቢወች ሆነው ስደተኞቹን ተቀብለው ማስቀመጣቸው የአብይና የወያኔ ድራማ መቅድም ነበር፡፡ አሁን የወያኔ ወራሪ ጦር ወደከተማዋ ሲጠጋ የአብይ ጦር ከተመዋን ለቅቆ እንዲወጣ ታዘዘ፡፡ ይህ ደግሞ የድራማው ክፍል አንድ ትእይንት ሆነ ማለት ነው፡፡ የአብይ ጦር ቆቦን ለቅቆ እንዲወጣ ሲታዘዝ ያ 60 ሽህ ስደተኛ ነው ቆቦ ከተማን የተቆጣጠራት፡፡ አሁን ያ ስደተኛ ነው በውስጥ የወያኔ አርበኝነቱ ከተማዋን እየዘረፈና ህዝቡን እየመራ እያስጨፈጨፈ ያለው፡፡
    ይህንን የአብይና የኦሮሙማ አዛዦች ድራማና ተንኮል የማይረዳ አማራ አለ ብለው ይገምታሉን?? እነርሱ አይታሙምኮ፡፡ ስለገመቱም ይመስላል የተበላ ድራማቸውን መስራታችውን የቀጠሉት፡፡
    ሌላው ሁሉ ይቅር፡፤ በጎን ሳያፈገፍግ ቦታ ይዞ እየተዋጋ ያለው የአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሽያ አያሳዝናቸውምን?? በእውነት የመንግስትነት ሀላፊነት ቢሰማቸው ኖሮ ማለትም ነገሩ ተንኮል ባይኖርበትና ድራማ ባይሆን ኖሮ ወያኔ የምትጠቀምባቸውን ምሽጎች የጦር ካምፖች፣ የማጓጓዣ ድልድዮችና መስመሮች የማዘዣ ጣቢያወች ወዘተ መንግስት ተብየው አያውቃቸውምን?? በእገረኛ ቢያስቸግር በአየር ሀይሉ መምታት አቅቶት ነውን ?? ሌላው ሁሉ ይቅር መንግስት ተብየው ስብስብ በተከዜ ወንዝ ላይ በጠለምትና በዋግ በኩል ያሎት ሁለቱ ድልድዮች የወራሪው ወያኔ ጦር የወረራ መተላለፊያ ቁልፍና ወሳኝ ድልድዮች ስለሆኑ በአየር ሀይሉ ተመትተው እንዲፈርሱ ማደረግ አቅቶት ነውን??
    ከሁሉም የሚያሳፍረው ደግሞ ወያኔ የፋኖን ምህረትየለሽነት ጠንቅቃ ስለምትረዳ የፋኖ ስምሪት ቀርቶ ስሙ እንዳይነሳ ያስደረገችው ከአብይ አህመድ ጋር ባላት የሴራ ስምምነት ነው፡፡ አለበለዚያማ ፋኖ ራሱን ችሎ በራሱ አዛዦች ወደ ዉጊያው እንዲገባ ቢደረግ ወያኔ ስትማረክ እንኳን በፋኖ መማረኳን የምትፈራበት እውነት ገሀድ ይወጣ ነበር፡፡ ምን ያደርጋል አብይ በተንኮል ያሰረውንና የሚያሳድደውን ፋኖን አምኖ ሊያሰልፈው ቀርቶ ስሙን መጥራት አስፈርቶት ፋኖን በዋና ጠላትነት መድቦት ይገኛል፡፡
    አብይ አህመድ አወቀም አላወቀም ለአማራ ህዝብ ፋኖ መገለጫ፣ ባህል፣ ወግ፣ እምነት፣ ስሪት፣ማንነትና ከፈጣሪ አምላኩ ቀጥሎ የአማራው ብቸኛ አለኝታው ነው፡፡ መጨረሻ ላይ ሁሉም ብሎ ብሎ ሲያቅተው ኦሮሙማ ወደመቃብሩ የሚወርደው በፋኖ(በአማራ ህዝባዊ ሀይል ነው)፡፡ ይህ ትንቢት አይደለም፡፡ በሂሳብ ተስልቶ ሊደረስበት የሚችል ቀላል ቀመር ነው፡፤ዋናው ምክንያቱም ለ46 ሚሊዮኑ የአማራ ህዝብ ብቸኛ አለኝታው ፋኖ ስለሆነ ነው፡፡ 46 ሚሊዮንን ህዝብ በጠላትነት የመደበ ሀይል መጨረሻው ምን ሊሆን እንደሚችል ራሳችሁ ገምቱት፡፡
    ከሶስትና አራት ወራቶች በፊት ከሱዳን በኩል አድርጎ ሌሊት ሌሊት ወደ ትግራይ ይበሩ የነበሩ አውሮፕላኖችን የኢኢትዮጵያ አየር ሀይል ሳያያቸው ቀርቶ ነውን፡፤ የሰሜን ጎንደር ህዝብ እኮ አይቷቸዋል፡፡ በረራው በተደጋጋሚ በየሌሊቱ እየተደረገ እንደሆነም ለመንግስት ተብየው አካል ህዝቡ ደጋግሞ ደጋግሞ ሪፖርት አድርጓል፡፤ መንግስት ምን አደረገ?? ህዝቡ በአይኑ ያያቸውን በረራወች አየር ሀይሉ በራደር አላያቸውምን??
    እንኳን አውሮፕላን አየር ሀይሉ ሳይፈቅድ “ወፍ” መብረር እንዳማይችል የኦሮሙማው አየር ሀይል አዛዥ በቴሌቪዥን ቀርቦ ደጋግሞ ደንፍቷልኮ!!!
    ለአማራ ምን ታስቦለት ነው ይህ ሁሉ የመንግስት ሻጥር?? ለነገሩ አማራ መንግስት አለውን???

  2. Amhara Hoy,

    Unless the federal government sends the army- Amhara militia and Fanno – to Tigray region and control supply lines to TPLF ragtag soldiers already in Amhara and Afar regions, it cannot end the invasion. How can the army -Amhara militia and Fanno – defend Amhara and Afar regions while TPLF is free to recruit, train, equip and mobilize without hiderance in its region? What a military strategy is it to let the enemy free to come and invade without the defense line extended to enemy lines? I think it’s politicians who’re scared of genocide accusations from TPLF that disallowed the army, Amhara militia and Fanno enter Tigray region to cut the supply lines to TPLF. Politicians should let the army to lead and reverse TPLF invasion. The only way to end the invasion is to enter Tigray to cut the TPLF army already in Amhara regions with a quick, selective and continuous military action in Tigray itself. Believe me! Tigray left to itself, there is no possibility to to end the invasion. They have nothing to defend because they are not attacked at home. So, they invade. Even a stupid can see what’s going on. Go to Tigray, guys.

Leave a Reply

Your email address will not be published.