የወልዲያ ከተማ ወቅታዊ ሁኔታ


ፎቶ፦ ከወልድያ ከተማ ኮሙኒኬሽን የማኅበራዊ ድረ-ገጽ

ከወልዲያ ከተማ ሸሽተው መርሳ ከተማ ከደረሱ በርካታ ነዋሪዎች ወደ ከተማዪቱ የሚመለሱም እንዳሉ ለዶይቸ ቬለ (DW) የዐይን እማኞች ተናገሩ። ከተማዋን ለቅቀው ከወጡት መካከል አንዳንዶች ዛሬ ከሰአት በኋላ ወደ ወልደያ በመመለስ ላይ ነበሩ ሲሉም አክለዋል። ከቀኑ ዐሥር ሰአት አካባቢ ዶይቸ ቬለ በስልክ ያነጋገራቸው አንድ የወልዲያ ነዋሪ «የባጃጅ እና የሰዎች እንቅስቃሴ» መኖሩን ተናግረዋል። መብራትም፣ ኔትወርክም እንዳለ እኚሁ ነዋሪ አክለዋል። በብዛት ሰዉ ከከተማዪቱ ወጥቶ የነበረው ትናንት ማታ እና ዛሬ ጠዋት እንደነበር፤ በአሁኑ ወቅት ግን ወደ ከተማዪቱ የሚገባም የሚወጣም እንዳለ የዐይን እማኙ ተናግረዋል።

መርሳ ከተማ እንደደረሱ የተናገሩ አንድ ግለሰብ ደግሞ ከራያ ቆቦ ተፈናቅለው በወልደያ በኩል መርሳ ከተማ መግባታቸውን ገልጠዋል። ከቅዳሜ አንስቶ ቀኑን ሙሉ በእግር እንደተጓዙ የተናገሩት እኚሁ ተፈናቃይ፦ ወልዲያ የገባሁት እሁድ ጠዋት ነው ብለዋል። እስከ ትናንት ድረስ በርቀት ተኩስ ይሰሙ አንደነበረም ነዋሪው አክለዋል።
ሌላኛው የወልዲያ ከተማ ነዋሪ መሆናቸውን ለዶይቸ ቬለ የተናገሩ ግለሰብ፦ ሰዎች «ተራ ወሬ ሰምተው ነው የኼዱት» እንጂ ከተማው ውስጥ ምንም የለም ብለዋል። ሆኖም «ከተማ ውስጥ ያለውን ነዋሪ በድምፅ ማጉያ እየዞረ የሚያረጋጋ የለም» ሲሉም አክለዋል።
ደሴ ከተማ እንደገቡ ለዶይቸ ቬለ የተናገሩ አንዲት ነዋሪ በበኩላቸው፦ «እስከ ሦስት ሺህ ብር ድረስ ከፍለው የመጡም አሉ» ብለዋል። «የራሳችን መኪና ስለነበረን ቀጥታ ነው የመጣነው» ሲሉ እንዴት ደሴ ከተማ እንደደረሱ አብራርተዋል። ደሴ ከተማ ተፈናቃዮችን ለማስተናገድ ከአቅሟ በላይ ነችም ብለዋል።
የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዲያቆን ተስፋሁን ባታብልን ጠቅሶ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በይፋዊ የፌስ ቡክ ገፁ ባሰራጨው ዘገባ «ወልድያ በጠላት እንደተያዘች የሚሰራጨው መረጃ ሐሰት መኾኑን ዞኑ አረጋግጧል» ብሏል።
DW

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአሜሪካ እርዳታ አምባገነኖችን ማጠናከሩ ይቁም - ግልፅ ደብዳቤ ለአሜሪካ መንግሥት ሃላፊዎችና ለአሜሪካ ሕዝብ

1 Comment

  1. Guys,

    Unless the federal government sends the army- Amhara militia and Fanno – to Tigray region and control supply lines to TPLF ragtag soldiers already in Amhara and Afar regions, it cannot end the invasion. How can the army -Amhara militia and Fanno – defend Amhara and Afar regions while TPLF is free to recruit, train, equip and mobilize without hiderance in its region? What a military strategy is it to let the enemy free to come and invade without the defense line extended to enemy lines? I think it’s politicians who’re scared of genocide accusations from TPLF that disallowed the army, Amhara militia and Fanno enter Tigray region to cut the supply lines to TPLF. Politicians should let the army to lead and reverse TPLF invasion. The only way to end the invasion is to enter Tigray to cut the TPLF army already in Amhara regions with a quick, selective and continuous military action in Tigray itself. Believe me! Tigray left to itself, there is no possibility to to end the invasion. They have nothing to defend because they are not attacked at home. So, they invade. Even a stupid can see what’s going on. Go to Tigray, guys.

Leave a Reply

Your email address will not be published.