ሕገ-መንግስቱን ለማሻሻል ለሚደረገው ሕዝባዊ ውይይት ይጠቅማሉ የምንላቸው ሐሳቦች (ከተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን)

የአገርን ጉዳይ ለፖለቲከኞች ብቻ መተው ኢትዮጵያን በጣም ጎድቷታል። ስለዚህ ሀገራችንን ከባሰ ጥፋት ለማዳን ማህበራዊ ድርጅቶችና ዜጎች የመፍትሔ አካል ለመሆን እንድንችል ሕገ-መንግሥቱን ለማሻሻል የሚያገለግሉ ግባዓቶችን የሚያዘጋጅ መድረክ (Forum) ተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን (Concerned Ethiopians) እንዲቋቋም ሐሳብ ያቀርባል። ይህ የሚቋቋመዉ መድረክ የምክክር ኮሚሽን ሥራውን ጀምሮ ሕዝባዊ ውይይቶችን በየዪኒቨርሲቲዎች እንደሚያደርግ ማሳወቁን ተከትሎ የቀረበ ጥሪ በመሆኑ፣ ዋናና አንኳር ጉዳዮችን የኢትዮጵያ ሕዝብ መወያየቱ ለኮሚሽኑ ሥራ ቀናነትና ፍጥነት የሚያግዘው ይሆናል።

በአገራችን የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የፍትሕ መዛባት፣ የሰላም ማጣት እና የድህነት መብዛት በጥቅሉ የችግሮቻችን መንስዔው የጎሣን ፖለቲካ ያወጀው ሕገ-መንግሥት ስለሆነ ተቀዳሚው ሥራ ሊሆን የሚገባው ይህን ሰነድ በማሻሻል የአፓርታይድ ሥርዓት ተወግዶ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን የሚሆንበትን ንድፍ ማዘጋጀት ነው።

በኢትዮጵያ የዘውድ፤ የወታደራዊ አምባገነንና የጎሣ የበላይነት አገዛዝ ስርዓቶች ተቀይረው፣ ኢትዮጵያ የሕዝብ፣ በሕዝብ፣ ለሕዝብ የሚያገለግል ሕዝባዊ የሪፐብሊክ መንግሥት እንድትመሠርት ፣ ሕዝቡ ዲሞክራሲና የሕግ የበላይነት የሚከበርባት ኢትዮጵያን ማየት መፈለጉን ሕዝባችን እስከዛሬ ባደረገው ተጋድሎ በግልጽ አሳይቷል።

እኛ ኢትዮጵያውያን የተሠራንበት ሥሪት የተለየ ነው። የራሳችንን ፊደል ቀርጸን ስነጽሑፋችንን ያዳበርን ፤ በጠላት አንገዛም ስንል ለጥቁር ሕዝብ ነጻነት ፈር ቀዳጅ የሆነዉን የአድዋ ድል አድራጊዎችም ነን። ዛሬም “እኔ በሕግ እንጅ አልገዛም በሰው” በማለት ለዚህ ሁሉ ችግር የዳረገንን ዘዉጌ ሕገ-መንግሥት ለማሻሻል በሙሉ ልብ እና በቁርጠኝነት ተነስተናል።

የጎሠኞች ክልል የዲሞክራሲ መቃብር ነው፣ ለሀገር ሕልውናም አደጋ ነው። ለሦስት አሥርተ-ዓመታት ግጭትና ቀውስም መንስዔው ይኸው የጎሣ ፖለቲካ ቁማር ያወጀው ሕገ-መንግሥት ነው።ሕገ-መንግሥቱ፤ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ሳትሆን ፤ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች መሬት ናት ይላል። ኢትዮዽያዊ የሚባል የጋራ ማንነትን አይጠቅስም። እውቅና የሚሰጠን በኢትዮዽያዊነት ሳይሆን በክልላዊነት ነው የሚል መነሻ አለው። የእኛ ልዕለ-ግብ ግን የከፋፋይ ሥርዓትን ለመለወጥ ነው። ዓላማችን ከጎሣ ፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ወደ የሁሉም ዜጎች እኩልነትና የሕግ የበላይነት የሚከበርባት፣ የሥልጣን ምንጩ የሕዝብ የሚሆንባት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮዽያን ለመገንባት የሚጥር የአገር-አድን ትግል ነው። በአሁኑ የአገር ማዳን ዘመቻ ወቅት ትኩረታችን ለሚቀጥለው ምርጫ ሳይሆን ለሚቀጥለው ትውልድ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኦርቶዶክስ ተዋህዶን መናዱ፣ ከሦስቱ ግንዶች አንዱ! - ዶ/ር ወንድሙ መኰንን

ዓላማችን ፀረ-ኢትዮዽያና ፀረ-ዲሞክራሲ የሆነውን የጎሠኛ ሕገ-መንግስት እና የጥላቻ ከፋፋይ ርዕዮተ-ዓለም እንዳይቀጥል የሚያደርግና በኢትዮዽያዊነት እሴቶች የሚተካ ነው።

አሁን ያለው ሕገ-መንግስት ለጎሣ መብትና እኩልነት የቆመ ሰነድ ሳይሆን ጎሣን ከጎሣ ጋር የሚያጋጭ እና ግጭቱም እንዳይቆም የሚያደርግ ነው። በኢትዮዽያዊ ዜግነት ጠንካራ አገራዊ ስሜት እንዳይኖር ሕገ-መንግስቱን የድርጅት ሥራ ማስፈፀሚያ በማድረግ በክልላዊ ሥርዓት ትግሬ ፣ አማራ ፣ ኦሮሞ ፣ ሶማሌ ፣ አፋር ፣ ሐረሬ… ወዘተ የሚባሉ ጥቃቅን፣ ደካማ መንግሥታት (mini states) እርስ በእርሳቸው ሲዋጉ እንዲኖሩ ቀምሮ የተነሳ አገር-በቀል ፀረ-ኢትዮዽያ ሰነድ ነው።

በሰሜን ኢትዮጲያ ላለፈው ሁለት ዓመት የተደረገው የእርስ በእርስ ጦርነት፤ የሰው እልቂትና የንብረት መጥፋት የጎሳ ፖለቲካዉ ያስከተለዉ ውጤት ነው። በተጨማሪም ይህ የጎሳ ፖለቲካ የወለደው ጥላቻ፣ እጅግ አሰቃቂ የዘር ተኮር ጥቃትና ዘር የማፅዳት ዘመቻ ማቆምያ አልገኝለት ብሎ እንዲቀጥል አድርጓል። ለዚህም ማሳያዉ በወላጋ የሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለዉ አሰቃቂና አሳዛኘ ጭፍጨፋ በቂ ማስረጃ ነዉ። በአሁኑ ስአት ሀገራችን ኢትዮጵያን የሚመራት የብልጽግና መንግስት ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ንፁኃን ወገኖቻችን ድረሱልን እያሉ ሲማፀኑ ከሞት አለማትረፉ ልብ የሚሰብር ነው። የሀገራችን ትምህርት ፖሊሲ ይህን አይነት ዘግናኝ ድርጊት እንኳን መፈፀም፣ መታሰብ እንደሌለበት ለወጣቶች ማስተማር ስላልቻለ ሊቀየር ይገባዋል።

አገር ወዳዱና ለውጥ ፈላጊው ኢትዮጵያዊ ያለው ምርጫ፣ በጎሣ መለያየቱን ትቶ ተባብሮ በመደራጀት በጎሣ ፖለቲካ ሥርዓት አልገዛም በማለት፣ ሕዝባዊ ተሳትፎ በማጠናከር በአንድ አገር ዜግነት መቆምና ያለውን የጎሣ ፖለቲካ የሚያስወገድ ስር-ነቀል ለውጥ ማምጣት ነው።

ሁሉም ኢትዮጲያዊ፤ መንግሥት፣ ፓርቲዎች፣ ፖለቲከኞችና አክቲቪስቶች ለውጥ እንዲያመጡ ጫና መፍጠር አለበት። እውነተኛና ጠንካራ የሆነ፣ የሕግ የበላይነትን የሚያረጋግጥ ሕገ መንግስት ለመቅረፅ የመጀመርያው ተግባራችን ሕገ-መንግሥቱን ማስተካከል ስለሆነ ይህንንም ለመተግበር ሀገር ወዳድ እና ተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን የሆን ሁሉ በመወያየት ለችግሩ የመፍትሔ አካል ለመሆን እንትጋ።

ተጨማሪ ያንብቡ:   የዐብይ አሕመድ መሰወርና የወያኔ ፕሮፓጋንዳ - መስፍን አረጋ

 

ተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን – Concerned Ethiopians

www.concernedethiopians.org

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንኳር ስህተቶች – አንድነት ይልቃል

አገርን የማያጸና ህገ መንግስት – ገብረ አማኑኤል

ህገ-ፓርቲ/ ኢህአዴግ  ህገ-ህዝብ አይደለም

የሕገ-መንግስት ትርጉም ጥያቄ አስተያዬት – ኢሳያስ ሃይለማሪያም

የተዓማኒነት ጉድለት ያለበት መንግስት… ከግርማ ሰይፉ ማሩ

ሕገመንግስት፤ መብት ተረጋግጧል ወይስ ተረግጧል (ተክለሚካኤል አበበ)

ፋኖ ላይ የዘመተው መንግስት ደባ…!

 

አንድ መንግስት የህዝብ ነዉ የሚባለዉ የህዝቡን ጥቅም እና ፍላጎት በፍትሀዊ መንገድ ማስተናገድ ሲችልነዉ – ሙላት በላይ

በህገመንግስቱና በሽግግሩ ቻርተር ይሁን ቢባል እንኳ (ቢባል እንኳ ነው እያልኩ ያለሁት) ወልቃይቶችና ራያዎች የአማራ ህዝብ አካላት ከመሆን የሚያግዳቸው አንዳችም ነገር የለም!!!

 

 

ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ስልጣናቸውን ማስረከብ አለባቸው!! የዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ የአቋም መግለጫ

 

1 Comment

  1. አስተያየቴ መግቢያውን በተመለከተ ነው።
    “ይህ የሚቋቋመዉ መድረክ የምክክር ኮሚሽን ሥራውን ጀምሮ ሕዝባዊ ውይይቶችን በየዪኒቨርሲቲዎች እንደሚያደርግ ማሳወቁን ተከትሎ የቀረበ ጥሪ በመሆኑ፣ ዋናና አንኳር ጉዳዮችን የኢትዮጵያ ሕዝብ መወያየቱ ለኮሚሽኑ ሥራ ቀናነትና ፍጥነት የሚያግዘው ይሆናል።”

    በተለይ “…ለኮሚሽኑ ሥራ ቀናነትና ፍጥነት የሚያግዘው ይሆናል።” የሚለው ባይጨመርበት የዚህ ጥሪ ሃሳብ ሁሉ መልካምና የተስተካከለ ትልቅ ፋይዳም ያለው ይሆን ነበር።
    የምክክር ኮሚሽን ብሎ አቢይ አህመድ ያቋቋመው ቡድን
    1. በጦርትነት ግርግር የሕልውና ሥጋት ወቅት የተቋቋመ
    2. አግላይ (ቢያንስ የአማራ ተወላጅ እንዳልተካተተበት ክስ ቀርቦ አልተስተባበለም)
    3. ስታሊኒስት ፖለቲከኞች የተሰገሰጉበት (የመቋቋሚያ ሕጉ ተጥሶ)
    4. አቢይ አህመድ የአካሄድ ጥሰት አድርጎ በጉልበት ተጨማሪ ሶስት ሰዎችን የጨመረበት
    የጨረባ ተዝካር ነው ተብሎ እንደተጋለጠ እየታወቀ በጥሪው መግቢያ ኮሚሺኑ እንደችግር ፈቺ ተቋም ተደርጎ መወሰዱ ይህንን የቀረበውን ጥሪ ራሱን የሚያጠለሸው ነው። ስታሊኒስቶች (ኦነግ፣ ሕወሃት፣ ብአዴን ወዘተ) ሕዝባዊ ውይይቶች ማካሄድ ይወዳሉ ነገር ግን በውይይቶቹ መጨረሻ በመጀመሪያ ወስነው የመጡትን ጉዳይ ነው የሚያስፈጽሙት። 40 አመት የኖርንበት መራራ እውነታ ነው። ስለዚህ አንጋፋ የኦነግና የሌላ ብሔርተኛ ፖለቲከኞች በተሰገሰጉበት አግላይና ሕገወጥ ኮሚሽን አማካኝነት አገር አፍራሹ ሕገመንግሥት ይሻሻላል ብሎ ማሰብ ከእባብ እንቁላል እርግብ እንዲፈለፈል መጠበቅ ነው።
    ሌላ ድብቅ ዓላማ ከሌለ በስተቀር (ለምሳሌ ኮሚሽኑን ሕጋዊ የማስመሰል/ቅቡልነት የማላበስ) ይሄ የተሰነቀረ መግቢያ ምንም አስፈላጊነት ስለሌለው ቢወጣና ጥሪው ታርሞ ቢቀርብ በጽሑፉ ለተካተተው ወርቅማ ዓላማ ስኬት ይበጃል እላለሁ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.