የመፈንቅለ ሲኖዶስ ስም ዝርዝር

“ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም”ይሉታል እንዲህ ነው፤ሲጀመር አቶ አካለወልድ(“አባ ሳዊሮስ”)… ግሩም አካለወልድ የሚባል ልጅ እንዳለው እየታወቀ እንዴት “አባ ሳዊሮስ” ተብሎ ጳጳስ ተደርጎ ተሾመ???
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕግ ወጥ ‘ሲመተ ጳጳሳት’ ጉዳይ:-
1. በሀገር ውስጥና ከሀገረ ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቾካይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።
2. መንግስት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ህጋዊ ሀላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
3. ምዕመናንን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም በላይ በንቃት በሀሳብና በፀሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል…።
#የመፈንቅለ ሲኖዶስ ስም ዝርዝር :-
1. አባ ተክለ ሃይማኖት …… የቀድሞ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ
2. አባ ገብረ እግዚአብሔር …… የአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት አስተዳዳሪ
3. አባ ሽኖዳ …… አለም ገና ኢየሱስ አስተዳዳሪ
4. አባ ወልደ ጊዮርጊስ …… ወለቴ ዮሐንስ አስተዳዳሪ
5. አባ ገብረ ኢየሱስ …… አለም ገና ሚካኤል አስተዳዳሪ
6. አባ ገብረማርያም ነጋሳ …… የኦሮምያ ቤተ ክህነት መስራች
7. አባ ጳውሎስ ከበደ …… የሐረር ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበረና በተሐድሶነት የተባረረ
8. አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ …… የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መጽሐፍ መምህር
ይቀጥላል…..!
—————————–
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት መንበረ ፓትርያርክ ብፅዑ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በረከታቸው ይደርብን..
አሜን(፫)

 አፈትላኪ ዜናዎች

ተጨማሪ ያንብቡ:  የክፉዎች ፍልሰት ይሁን (Let Exodus of Evil be) - ሰማነህ ታ. ጀመረ-ዖታዋ፤ ካናዳ፤

2 Comments

  1. ጎበዝ!
    ጌታቸው ረዳ የተባለ የአክሱም ኢትዮጵያዊ ላለፉት 30 አመት ያለመታከት ባንዳን( የኦሮሞን፤የትግሬን) ሲፋለም እስከ ዛሬ የኖረ ወንድማችን ነው፡፡ የህወአትን ታላቁን ሴራ ቀድሞ የሚያሳውቀን ይኸው ወንድም ነው ነገር ግን ስራው በብዙ ኢትዮጵያውያን የሚታወቅ አይደለም ብዙ ደክሞ የሚያዘጋጀው ” ethiopian semay” የሚል የድር ገጸ ስላለው ጥልቅ የሆነ ጽሁፉን ለማንበብና ለስራው እውቅና ለመስጠት እየገባን ብናነበው ለሌሎች ብናስተላልፈው እኛም አገርም ተጠቃሚ እንሆናለን የሚል እምነት አለኝ፡፡አመሰግናለሁ

  2. አይ ኢትዮጵያ አይ መከራሽ ቀሲስ በላይ እስላሙን አራጁን ጁዋር መሀመድን የማታውቅ ኦርቶዶክስ እኔም አላውቃትም ብሎን ነበር አሁን ደግሞ ምን ሁኖ ይሆን?

Leave a Reply

Your email address will not be published.