ጦርነት ማዳፈን ሠላም ማስፈን እንዴት ይሆናል ?  

LUUTDZ4TQBMHPEBY3PTGFYXTFI 1 1 1 1 1 1 1

ኢትዮጵያ ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ ግንቦት 20 ይዞት የመጣዉ የማይቋጭ መከራ  ለኢህአዴግ የሥልጣን መከዳ በመሆን በህዝብ እና በአገር ላይ ለደረሰዉ ፖለቲካ አመጣሽ የሰለሳ ዓመታት  ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆንም መከላከያ ሆኖታል ፡፡

ላለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት ከፍተኛ የአገር ክህደት ፣ የዜጎች በማንታቸዉ እና ኢትዮጵያዊ በመሆናቸዉ ፣ በዕምነት እና አመለካከት የአገር ጉዳይ የህልዉና ጉዳይ መሆኑን በመረዳታቸዉ  ፍጂት፣ ዕልቂት ፣ ዕንግልት፣ ስደት ፣ መፈናቀል ፣ ዉርደት እና ባርነት አስተናግደዋል ፡፡

ኢትዮጵያም ሆነ ኢትዮጵያዉያን ስለ አገር አንድነት እና ሉዓላዊነት ፤ ስለህዝቦች አንድነት እና ደህንነት ህዝባዊ እና ብሄራዊ  ቅንነት   እና ቁርጠኝነት ያለዉ  የፖለቲካ ተቋም መሪ እና ዘዋሪ ባለማግኘት እና ባለመለየት መሪ አልባ በመሆን አሁን ከደረስነበት ተደርሷል፡፡

ኢህአዴግ ከሽግግር ዘመን ጅምር አስካዘሬ መደመር ከህዝብ እና ከብሄራዊ ፍላጎት እና ጥቀም በተቃራኒ በመሄድ የቁራ ፖለቲካ ሲያራምድ ከራሱ ዉጭ የሚስተጋባዉን  መከራ እና ዋይታ  እንደ ደስታ እና ርካታ ሲወስደዉ ማየት ዛሬ ላይ አዲስ ሊሆን ባልተገባ ነበር ፡፡

የእኛ አገር ፖለቲከኞች  ስለ ህዝብ እና አገር እየተናገሩ  ለዘመናት ሲምሉ ፤ሲገዘቱ  ግን የህዝብ መከራ ሰቆቃ ከማይሰማበት የቁራ ዛፍ ተጠልለዉ ኢትዮጵያዊነት እና ብሄራዊ አንድነት ይመጣል ብለዉ ተስፋ ሲያደርጉ ማየት በእጂጉ የሚያሳዝነዉ እና ከኢትዮጵያ ግልፅ ጠላቶች ይልቅ ጠላቶች ወይም ተባባሪዎች ሆነዋል ፡፡

በኢህአዴግ ህገ መንግስት እና በኢህአዴግ  የጥላቻ እና ከፋፋይ የፖለቲካ  መስመር   በኢትዮጵያ ሰማይ ስር የሆኑት እና የተደረጉትን በአገር እና በህዝብ ላይ የተፈፀሙ ደባዎች  አለማስታወስ  እና ከዚህ አለመመለስ እየታየ በጥፋት ላይ ጥፋት በሚደራረብባት አገር መናጆ የሆኑ ፖለቲካ ድርጂቶች ኢትዮጵያን ከሚገዘግዟት በላይ ተጠያቂዎች ናቸዉ ፡፡

ለዓመታት በህገ  ኢህአዴግ  ሽፋን በክልል አደረጃጀት እና በህዝብ መለያየት ለደረሱ ሠባዊ እና ቁሳዊ ጥፋቶች ብሄራዊ ጥፋት እና ክህደት መሆኑን እያወቁ  በዝምታም ሆነ በይሁንታ ያለፉ ህዝብን እንወክላለን የሚሉ ፖለቲከኞች ከህዝብ እና ከአገር ይልቅ ተመሳስሎ መኖርን መምረጣቸዉ ከህዝብ መኃል ሆነዉ የቁራ ጩኸት ቢያሰሙ ከቁራ ዛፍ ስር መሸጎጣቸዉ ከታሪክ እና ከተዉልድ ተጠያቂነት አያድናቸዉም ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ላይ የክተት ዘመቻ

ሁላችንም እንደምናዉቀዉ ህዝብ በሁሉም ነገር ከፊት ሆኖ መሪ ነን የሚሉት ከኋላ ሆነዉ  ለአገር እና ለነፃነት የተከፈሉ ዋጋዎች እጂግ ብዙ ናቸዉ ፡፡ ለወትሮዉ ዞትር በአገር እና በህዝብ ጉዳይ ኢትዮጵያዉያን መሪዎች ከህዝብ እና ከአገር በፊት ራሳቸዉን  በኢትዮጵያዊነት ልክ ከጠላት ፊት ቆመዋል ፡፡ ለዚህም የዓደዋዉን ፣ የካራ ማራዉን ጦርነት እና የጦር ዉሎ ማስታወስ በቂ ነዉ ፡፡ ሚኒሊክ በዓደዋ ፤ መንግስቱ በካራ ማራ…… በጦርነት  ግንባር ተገኝተዋል ፡፡ ወደ እኛ ዘመን ስንመጣ በኢትዮጵ ፤ኤርትራ የኢትዮጵያ ህዝብ እናት አገር ወይም ሞት ብሎ ያለ መሪ ወደ ጦር አዉድ ተምሞ  በተከፈለዉ የህይወት ፣ደም ፣ አካል …ዋጋ ዉጤቱ ምን እንደሆነ  የቅርብ ዘመናት መሪር ትዝታ ነዉ ፡፡

ይህ አልበቃ ብሎ  ትህነግ /ኢህአዴግ ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም.  ከታዘልኩ አልወርድም በሚል አባዜ ወደ ነፃ አዉጭነት ራሱን መልሶ የፈረደባቸዉ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ፤ዓማራነት ተዘመተባቸዉ ፡፡ ይህም በመከላከያዉ ለይቶ ማጥቃት ፣ ቀጥሎ በጎንደር ፣በወሎ ፣በሸዋ……ወረራራ በማድረግ ህዝቡን በማወረድ ፣በማሳደድ እና  በማስወገድ የግዛት ማስፋፋት እና  አገረ ትግራይ መገንባት በሚል ዕብሪት በታሪክ የማይታወቅ ዘግናኝ ዕልቂት ፣ ሞት ፣ ምዝበራ እና የሠባዊ መብት ወንጀል በኢትዮጵያ ህዝብ በሆነዉ ዓማራ እና አፋር ላይ ተፈፅሟል ፡፡

በዚህ ራስን የመከለካከል እና ነፃ  የማዉጣት የህልዉና ተጋድሎ  ሁሉም ኢትዮጵያዊያዉያን ይነስም ይብዛ ፤ በተለይም ዓማራ እና አፋር የመከራዉ እና የጦርነቱ ዒላማ እና  ሞት የተፈረደበት ህዝብ  ማቄን ጨርቄን ሳይል አስካፍንጫዉ የታጠቀ ጠላት ጋር በፉፁም ብሄራዊ እና ህዝባዊ ወኔ በመተናነቅ  ተደጋጋሚ እና ዕልህ አስጨራሽ  ትግል ኢትዮጵያ ፣ኢትዮጵያዉያን እና የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች አገር እና ህዝብ ከክህደት አዋላጆች እና አራማጆች ተከላክለዋል ፡፡

ኢትዮጵያን ያዳነ የኢትዮጵያ ጠላቶችም አድኗል ፡፡ በመዳናቸዉም እንደገና ኢትዮጵያዉያን እና ኢትዮጵያን ለማቁሰል  ሲንደረደሩ ማየት “ባሪያን ነፃ ያወጣ ጌታዉን ነፃ ያወጣል ” እንዲሉ የዓማራ ህዝብ እና የአብራኩ ክፋዮች  የክልሉ መደበኛ የፀጥታ ኃይል ፤ ፋኖ  እና ሁሉም በሚባል“ የትናንት  እና ከድል ማግስት ጠላት የሆኑትንም ” ለዛሬ ማድረሱ ጀግና የባሪያን ጌታ ብቻ ሳይሆን ጠላትንም ታድጓል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብልጽግና ከወያኔ ጋር ቢደራደር ምንድን ነው የሚኮነው ? - ግርማ ካሳ

ዛሬ ጦርነት አዳፍኖ ሠላም ሠላም ሲባል ለሠላም ፤ ለአገር አንድነት እና ለህዝብ ሉዓላዊነት የተከፈለዉን ዋጋ ፤ ጀግኖችን እና የጠፋዉን ጥፋት በማደባበስ ሳይሆን በግልፅ በመንቀስ እና በማወደስ  ለሁሉም ዕዉቅና እና ተጠያቂነትን ማስፈን ግድ ይሆናል ፡፡

ከጦርነት መሸሽ ጦርነት አያስቀርም ፡፡ ይህ ለአገር እና ህዝብ ዘላቂ መፍትሄ ከሚኖረዉ ይልቅ አጠያያቂ ጉዳይ ይዞ ይቀጥላል ለምን ካሉ የተጎዳ ባልተካሰበት ፤ የጎዳ ባልተጠየቀበት ይድረስ ይድረስ ከወንጀል እና ከታሪክ ተጠያቂነት አያድንም ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የዓማራ ህዝብ ለአለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት አገር አልባ እና ባይተዋር በአገሩ ሲሆን እና ለደረሰበት ዕልቂት ቀድሞ የነበረዉን ብሄራዊ እና ህዝባዊ የአገር መከላከያ በማፍረስ ኢህአዴግ አርሶ አደሩ በነፍስ ወከፍ  ከጉርሱ እና ልብሱ ቀንሶ የገዛዉን መሳሪያ ቀምቶ ባዶ እጁን ቁም ቅምጥ ሲነሳ መኖሩ ተርስቶ ዳግም በዘመናዊ ጦር መሳሪያ ለሠላሳ ዓመት በተደረገ ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና ዓማራን ለማሳነስ ዳግም ቀጥታ ወረራ እና ምዝበራ ማድረግ እና ይህን ተከትሎ በተደረገ የህዝብ የመከላከል ተፈጥሯዊ መብት የዓማራ ህዝብ ራሱን እና አገሩን የመከላከል ሠባዊ እና ኢትዮጵያዊ መበቱን ከማንም የሚጠብቅ መሆን የለበትም ፡፡

በአንድነት ክንድ እና በፅናት ህልዉናዉን ለማስቀጠል ባይዋደቅ ኖሮ ዛሬ አገርም ነጻነትም ጠፍቶ ጭራሽ ተንበርካኪ በሆን ነበር ፡፡

የዓማራ ህዝብ የኢትዮጵያን አንድነት እና ሉዓላዊነት ላይ ካለዉ እና ከሚኖረዉ ቁርጠኛ አቋም አኩያ የተረፈችዉን ኢትዮጵለማስቀጠልም ሆነ ኢትዮጵያዊነትን ለማረጋገጥ የኢትዮጵያ  ህዝብ በተለይም ዓማራ ከሞት ፣ ባርነት እና ስደት ቀንበር ለመላቀቅ ብቸኛዉ መንገድ ከምንጊዜዉም በላይ ለራሱ እና ለአገሩ ዘብ መቆም አለበት ፡፡ ምንጊዜም ለራስ እና ለአገር ዘብ መቆም የነፃነት ዋጋ ነዉ ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አዬነው ጽናቱን የጴጥሮስ ህይወቱን። (ሥርጉተ ሥላሴ)

ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያን መዳኛቸዉ ራሳቸዉ እና ረሳቸዉ ብቻ ናቸዉ ፡፡ የኢትዮጵያዉያን ችግራችን ጠላት እንደማይተኛ ሳናዉቅ ፤ የእኛ መዘናጋት እና ህብረት ማጣት ከምንም በላይ ሊያሳስበን ይገባል፡፡

ሠላም ሆነ ጦርነት ሠወች በሚሉት የሚኖር ሳይሆን  ፍትህ እና ዕኩልነት በጠፋበት ፤ የግል እና የቡድን ጥቅም እና ፍላጎት በበዛበት ፤ ሠርቶ መኖር በሠዎች በጎ ፈቃድ በሚሆንበት ፤ በሀይወት የመኖር እና ዛሬ ዓለም የሰዉ ልጆች መንደር በሚባልበት በአገር የዜግነት ክብር እና መብት መጥፋት፤ ለአገራቸዉ እና ለራሳቸዉ ህዝብ ህልዉና ልዕልና ዋጋ የከፈሉበት ሊያሸልም ሲገባ እስር እና ዕንግልት………. ፤ ለህዝብ እና ለአገር ቅድሚያ እና ክብር አለመስጠት ከዚያ ላይ ለግል እና ቡድን ጥቅም መሯሯጥ በሚታይባት ምድር ስለ ሠላም ዋጋ ማነብነብ  ከልብ ይሆናል ብሎ ማሰብ የጦርነት ምንነት ማሳነስ ነዉ ፡፡ ርኃብ በርኃብ ፤ ስደት በስደት፣ ሞትበሞት….. “ደም በደም ለማንጻት ” እንደመሞከር ነዉ ፡፡

የጥላቻ መንፈስ አርግዞ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማሳነስ እና በማኮሰስ የሚደረገዉ ጥላቻ ወለድ ዘመቻ መነሻ እና መዳረሻ የሆነዉ ኅገ-ኢህአዴግ ባለበት ስለ ጦርነት እና ሠላም የሚወራዉ በቁራ ፖለቲካ ጥላ ስር ብቻ ነዉ ፡፡ ይህም “ቁራ ከራሱ ድምፅ ዉጭ የሚጥመዉ የለም ”እንዲባል ሠላምም ፤ጦርነትም የሚሉት ከመንደራቸዉ ዉጭ መንደር የማይታቸዉ ቀንድ አዉጦች ብቻ ናቸዉ ፡፡

በአገራችን በአሁኑ ጊዜ ሲደማመር የደረሰዉ ፈርጀ ብዙ የሠላም እና የመኖር ችግር በተለምዶ ጦርነት ከሚባለዉ በላይ ጦርነት መሆኑን በመረዳት ዕዉነት እና ርትዕ እንዲኖር ከመስራት ዉጭ አማራጭ ጦርነት ማዳፈን ሠላም ማስፈን አይሆንም ፡፡ጦርነትን ማዳፈንም  ሆነ መሸሽ ጦርነትን አያስቀርም ፤ ሠላምም አያስገኝም ፡፡

“የአገር እና ህዝብ ብቸኛ መዳኛ ዕዉነተኛ የቁርጥ ቀን ልጆች የህብረት ክንድ ብቻ ነዉ ፡፡”

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

Allen Amber!

2 Comments

  1. ጌቾ እንደዛ በስድብ አጥረግርገኻቸው አለቃቸው ሁነህ ቁጭ አልክ? እንዴት ነው ፊት ለፊትህ የሚቆሙት ማናቸውም፡፡ ስለ አብይ/ባጫ ደበሌ/ለገሰ ጫፎ/ አዳነች አቤቤ፤ጌዲዎን ጢሞትዎስ፤ሬዱዋን ሁሴን፤ብርሃኑ ጁላ፤ … ማንን አልተናገርከውም እድሜ ለዩ ቲዩብ እያየን እንስቃለን እነዚህ ክብር የሌላቸው ገና ካፖርትህን አሸክመህ ይከተሉሃል ጫማህ ሲፈታም ተሽቀዳድመው ያስሩልሃል ስለ ክብራቸው ብዙም አይገዳቸውም፡፡

  2. እኔ የማዝነው በዚህም በዚያም ተሰልፈው ለሃገር ለወገን ነው እየተባሉ ህይወታቸው ላለፈው ወገኖቼ ነው፡፡ ከህዋላ ሆነው የሚገፉን ያኔም አሁንም ዞረው ቂጥ በመግጠም ሌላ የፓለቲካ ዘዴ እየቀየሱና መልካቸውን እየቀያየሩ ለመኖር ብልሃት መፈለጋቸው የተለመደ ነው፡፡ ትላንት ሲኦል ድረስ ወርደን ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን ያለው የወያኔ ወስላታ ፓለቲከኛ መለስ ብሎ በግጭቱ ጊዜ የሰጠውን ቃለ መጠየቅና ፉከራ ለተመለከተ ወቸው ጉድ እብድም ለካ ልብ ይገዛል ያሰኛል፡፡ አሁን አቶ ጌታቸው በአሜሪካ ተመርጦ የጊዜው ባለስልጣን ሆኗል፡፡ ይሁን መቸስ በራሳችን ማሰብና መኖር ከተቀማን ዘመን አልፏል፡፡ የሚገርመው ግን ዛሬ በሰጠው የንባብ መግለጫ ላይ በአንድ በኩል እርቅና ሰላምን ሲናገር በሌላው ጎን የትግራይ መሬት፤ አማራ፤ የኤርትራ ጦር እያለ ሲቀባጥር መስማት በእጅጉ ያማል፡፡ ከ 1ሚሊዪን በላይ ሰው ያለቀበት የዶ/ር አብይና የወያኔ ፍልሚያ የጎዳው ትግራይን፤ አፋራንና አማራን ነው፡፡ ሌላው ወገን ደግሞ እኛ ስንቧቀስ ዝርፊያውንና ልማቱን ከተንኮል ጋር ተያይዞታል፡፡ የኤርትራ ጦር ትግራይ ውስጥ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ካለ እንዲወጣ ማድረግ ያለበት የፌዴራል መንግስቱ ነው፡፡ አይ ወያኔ በባድሜ ዙሪያ ከሆነ የሚያለቅስው ያበቃ ያለቀ ነገር ነው፡፡ ያኔ ኤርትራ ሃገር ሆናለችንና እወቁልን እያላችሁ በኣለም መድረክ ላይ ከሻቢያ ቀድማችሁ ስትለፉ ይህ እንደሚመጣ መገመት እንዴት ተሳናችሁ? ያኔ የአሰብን ወደብ ግመሎች ማጠጫ ይሆናል እያላችሁ ስታፌዙ የቀይ ባህር ውሃ ግመሎች ሊጠጡት የማይችሉት የጨው ውሃ እንደሆነ ጠፍቷችሁ ይሆን? ስለሆነም በባድሜ ጉዳይ ማልቀሱ በተደፋ ውሃ እንደማልቀስ ይቆጠራል፡፡ ፋይሉ ተዘግቷል፡፡ ሌላው ምእራብና ምስራቅ ትግራይ የምትሉት የቱን ነው? በግድ በ 27 ኣመቱ ሰቆቃ ያየውን የራያና የጠለምት እንዲሁም የወልቃይትን መሬት ነው? አብሮ መኖር ይቻላል፡፡ ዳግመኛ ግን የትግራይ መሬት ጋር ይካለላል ብሎ ማሰብ ዳግም እልቂትን ለማስከት እንጂ ሌላ ትርፍ የለውም፡፡ ስለሆነም የጌታቸው ንግግር ባንድ በኩል ስንጥር በሌላ በኩል የዝንባባ ዝንጣፌ የያዘ ዝብርቅ ንግግር ነው፡፡ ህግ ቢኖር እኮ ወያኔ በትግራይ ህዝብ ፊት ፍርድ ባገኘ ነበር፡፡ ህግ ግን የለም፡፡ ጌታቸውም የተሾመው በጠ/ሚ አብይ በጎ ፈቃድ አይደለም፡፡ በአሜሪካ እጅ ጥምዘዛ እንጂ! እንግዲህ ወያኔና የአማራ መሪዎች እርስ በእርሳቸው ሲሸራደድ ኦነግ አፍራሽ ሥራውን እየሰራ ይገኛል፡፡
    የጠ/ሚሩ መንግስት ወልጋዳና ለሰዎች መብት ግድ የማይሰጠው ልክ እንደ ወያኔ በዘርና በቋንቋ ተቀይዶ በወረፋ ህዝብን የሚያሰቃይና የሚግጥ መንግስት ነው፡፡ ጠ/ሚሩ በጊዜአዊም ሆነ በምርጫ ወደ ስልጣን ከመጣ ወዲህ የሞቱ ሰዎችን ቁጥርና እነማን እንደሞቱ በዝርዝር ቢታይ ሚስጢር ነው የሚባለው አደባባይ ይወጣል፡፡ ዛሬ የሚታሰሩት፤ የሚታፈኑት፤ ተደብድበው የሚለቀቁት፤ የሚገደሉት እነማን ናቸው? ምን ስላደረጉስ ነው ይህ ሁሉ ወከባና ግድያ የሚደርስባቸው? ለምንስ ነው መንግስት ነኝ ያለ እንደ ተራ ሌባ ቢሮ ሰብሮ የሚዲያ ቁሳቁሶችን የሚሰርቀው? እንዴት ነው በቀኑ ካህን በአዲስ አበባ ላይ በድንጋይ ተቀጥቅጦ የሚሞተው? ይህ በእቅድና በፕላን የሚመራ እንጂ በነሲብ በቀን ወሮበሎች የሚደረግ ተግባር አይደለም፡፡ ካህኑ የተገደለው ቤ/ክርስቲያንን ለማዳከም፤ ማን ጠንካራ ነው ማን ይመታ ተብሎ በተጠና መልኩ እንጂ ዝም ብሎ አልፎ ከሚሄድ ሰው ጋር ስለተጋጩ አይደለም የተገደሉት፡፡ መንጋውን ለመበተን ጠባቂውን ምታ በሚል የኦሮሞ ጭፍን ፓለቲከኞች ፈሊጥ እንጂ፡፡ የሚያሳዝነው ፓሊስ እንኳን ምርመራ ለማድረግ አለመቻሉ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ፓሊስ ጋ ሲኬድ ኦ ድርጊቱ የሆነው ኦሮሚያ ክልል ስለሆነ ለኦሮሚያ ክልል አመልክቱ፤ ኦሮሚያ ፓሊስ ስኬድ ለአዲስ አበባ ፓሊስ አመልክቱ እየተባሉ ሰው በግፍ ተገድሎ ያደለው ተለቅሶለት ይቀበራል፤ ሌላውን ጅብ ይበላዋል፡፡ ይህ ነው የጠ/ሚሩ አመራር፡፡ ተደመሩ እያለ የሚያስቀንስ፡፡
    ግራም ነፈሰ ቀኝ ለጊዜው ሊመስል ይችል ይሆናል እንጂ ገዳይና አስገዳይ በወረፋቸው ሥፍራ ይይዛሉ፡፡ በታሪክ ያየነው በሰው ደም እጃቸው የጨቀዬ ሁሉ መጨረሻቸው የከፋ ሲሆን ነው፡፡ ግ ን ማን ካለፈው የቅርብ ቀን ታሪካችን ይማራል፡፡ ዝም ብሎ መወሻከትና የዛሬ 100 ኣመት አማራ ክርስቲያን አድርጎ አጥምቆኛል ስሜንም ቀይሯል እያለ ምኑንም የማያውቀውን ሰው በዘሩ እየመረጠ ይገላል፡፡ የወያኔና የኦነግ ሸኔ ጥምረት ለአማራ ህዝብ የመከራ ዝናብ እንደሆነ አይተናል አሁንም አያቋርጥም፡፡ ከ 50 ኣመት በላይ በተንኮልና በደም የሰከሩ የወያኔና የኦነግ መሪዎችን ስለ ሰው ስብእናና አብሮ መኖር ይረዳሉ፤ ይለወጣሉ ብሎ ማሰብ ነፎዝ መሆን ነው፡፡ ጌታቸው የወያኔ አንድ የተንኮል ኮረጆ ነው፡፡ ከጠ/ሚሩም ሆነ ከሌሎች ጋር ለመስራት አይቻለውም፡፡ ሁለቱም የየግል አጀንዳ ይዘው ስለሚጓዙ የሚገናኙበት መንገድ የለም፡፡ ይተላለፋሉ፤ ወይ ይጠላለፋሉ፡፡ የሃበሻ ፓለቲካ የመበላላት ፓለቲካ ነው የምንለውም ያለፈን ዳስሰን አሁን በምድሪቱ ላይ ካለው የከፋ የአፓርታይድ ፓለቲካ በመነሳት እንጂ የማንኛውም ዘርና ቋንቋ ጥላቻ የለብንም፡፡ የኦሮሞ ፓለቲከኞች ቀጥሉ ግደሉ አስገድሉ፤ ተበቀሉ፤ ኦሮሚያንም መስርቱ ይመቻችሁ፡፡ በሰው ደም የሚነግድ ሁሉ መጨረሻቸው መሳቂያና ውዳቂ መሆን ነው፡፡ በጊዜው ሰካራም እንደ ረገጠው ጣሳ ትሆናላችሁ፡፡
    በመጨረሻም እናንተ የአማራ አመራር ነን የምትሉ የእድሜ ልክ ተለጣፊዎች እስከ መቼ ነው ዝምታችሁ? እንዴት ሰው በሃገሩ ለዚያውም ካህን በድንጋይ ተቀጥቅጦ ይገደላል? አሁን በዚህም በዚያም ፋኖ ትጥቅ ይፍታ፤ እከሌ እንዲህ ይበል እያላችሁ ሰው በባዶ እጅ አታስጨርሱ፡፡ በወሎ፤ በጎንደር፤ በሰሜን ሽዋ፤ በአፋር የሆነው እንዴት ትምህርት አይሆናችሁም?፡ ሆን ተብሎ ወያኔ ሃገር እንዲያፈራርስ መንገድን የከፈተለት የዶ/ር አብይ መንግስት ነው፡፡ ሌላው ሁሉ ማጣጫ ፓለቲካ ነው፡፡ ከገባን ወያኔ ሱዳን የኢትዮጵያን ህጋዊ መሬት ተቆጣጥራ አንድም ቀን በዚህ ሁሉ ድንፋታቸው መውጣት አለባት አለማለታቸው ከሱዳን ጋር ያላቸውን የቆየ ሽርክና ያሳያል፡፡ የወያኔ የዝንተ አለም ጠላት አማራና የኤርትራ መንግስት ነው፡፡ ይህም አለቆቻቸው ከሚግቷቸው የትርክት ፓለቲካ የተወሰደ ነው፡፡ የኦሮሞና የወያኔ መስማማትም ለሃገራችን ሰላም ሳይሆን መከራን የሚያዘንብ የሁለት አጥፊዎች ጥምረት ነው፡፡ እድሜ ያለው ይህን ቃል ይመዝን፡፡ በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.