ታገል ሰይፉ፡ ኢሕአዴግ ካምፕ ውስጥ ያደገው አውሬ

“ራሱን መከላከል የማይችል አብዮት እርባና የለውም”
ሌዋታን…ኢ. ህ. አ. ዴ. ግ. ካምፕ ውስጥ ያደገው አውሬ

ከዳንኤል ገዛኽኝ አትላንታ

ከሰሞኑ ገጣሚ ታገል ሰይፉ ሃገር ቤት እየታተመ ከሚሰራጨው ቁም ነገር መጽሄት ጋር አንድ ቃለ ምልልስ አድርጎዋል። በቃለምልልሱ ውስጥም ታገል ብዙ አሳፋሪ አንገት የሚያስደፉ ነገሮችን መናገሩን አንብቤ ከልቤ አዝኛለሁ። በተመሳሳይ የታገል ምልልስ አንጀታቸውን ያሳረራቸው…ወሽመጣቸውን የቆረጣቸው ግለሰቦች ቁጣቸውን በታገል ላይ ይገልጻሉ። አሁንም በታገል ላይ ያላቸውን ቁጣ በርካታዎቹ እየገለጹ ነው። በመሰረቱ ይህ አሁን ስለሆነ እንጂ ቀደም ሲልም ታገል ሰይፉ በህይወቱ ገንዘብ የማግኛ መንገዶችን በመተለም ስራዎቹን የሚሰራ ገጣሚ ነው። እርግጥ ነው ሰው ለሚሰራው ስራ ዋጋ ቢያስፈልገውም ታገል ግን ለገንዘብ ተፈጥሮ ለገንዘብ ህሊናውን የሸቀጠ መሆኑን ለማሳየት የተጠቀምኩበት ነው። ለነገሩ በመሃል ገጣሚነቱን እርግፍ አድርጎ በመተው ወደ ወግ እና ኩመዳ እልም ብሎ ገብቶም ነበረ አልተሳካለትም እንጂ።
ለነገሩ ቁም ነገር መጽሄት ላይ ስለሰጠው ነገር ከማለቴ ይልቅ ታገልን የማውቀውን ያህል በጥቂቱ ልበል። ታገል ሰይፉ ገና የ ኤለመንተሪ ተማሪ እያለ ነበረ የመጀመሪያውን የግጥም መድብል መጽሃፉን የጻፈው። እናም ያ መጽሃፍ ግን የራሱ ሂደት እና ታሪክ ነበረው። ነገሩ እንዲህ ነው መጽሃፉን ከጻፈ በሁዋላ ቤተሰቦቹ የማሳተም አቅም ስላልነበራቸው በወቅቱ የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ያየህ ይራድ ቅጣው በሆነ አጋጣሚ የታገልን አብዮታዊ ስሜት ቀመስ በመንግስት ጋዜጣ ላይ ወጥቶ በማየታቸው ታገልንም እንደዚያው በአጋጣሚ ሲያገኙት ምን ሊደረግለት እንደሚፈልግ ይጠይቁታል። ታገልም መጽሃፉን እንዲያሳትሙለት ይጠይቃል። እንዲያሳትሙለት ይጠይቃል።
በዚህ መሰረት ሚኒስትሩ ብጣሽ ወረቀት ላይ በመጻፍ የታገል መጽሃፍ እንዲታተምለት ለብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ቤት ይልካሉ። ወዲያው የታገል የመጀመሪያ መጽሃፍ ብርሃን እና ሰላም ለህትመት ይገባ እና ታትሞ ይጠናቀቃል። እናም ለታገል እባት እና ለታገል እንድ መል ዕክት ይደርሳል። መጽሃፋቸው ታትሞ በማለቁ ህትመቱን እንዲረከቡ ይገለጽላቸዋል። ታገል እና አባቱም በፍጥነት ከማተሚያ ቤቱ ሲገኙ የማተሚያ ቤቱ ሃላፊዎች ገንዘቡን ለህትመት የሚከፈለውን ከፍለው መጽሃፋቸውን እንዲረከቡ ይነግሩዋቸዋል። ሁኔታው በመንግስት ደመወዝ ለሚተዳደረው የታገል ቤተሰብ ትልቅ ድንጋጤን ይፈጥራል። ነገሩ እየተካረረ ሄዶ ታገል እና አባቱ እስከመታሰር ፍርድ ቤትም እስከ መቅረብ ይደርሳሉ በሁዋላ አባቱ ከደመወዛቸው እየተቆረጠ እንዲከፍሉ ይወሰናል። ታገል እንግዲ በቀደመው ዘመን ነበረ ከአብዮቱ ጎን ተሰልፎ የበኩሉን አስተዋጾ ሲያደርግ የቆየው።
ይህ አለፈ እና ወያኔ ሲመጣ ታገል የአስተላለፍ ለውጥ ለማድረግ ቀፎውን አትንኩት የምትለውን መጽሃፉን አሳትሞ አድፍጦ ሲጠብቅ ቆየ። በሁዋላም ሃምሳ አለቃ ገብሩን ይዞ ኢትዮጲያ ሬድዮ ሰተት ብሎ ገባ። ትንሽ ተረጋግቶ ደግሞ ሌዋታን ሲል የቀረቀበውን እንቶ ፈንቶ ግን በ አቅሙ ወያኔን ሊሞግት እና ሊያብጠለጥል የሞከረበትን ልብ ወለዳዊ ትረካ ያለውን መጽሃፉን አሳተመ። ይህ መጽሃፍ ብዙም ሽያጭ ባያገኝም ግን በተለይ እንደ ንኡስ አርስት ኢህአዴግ ካምፕ ውስጥ ያደገው አውሬ የሚለው ወያኔን የሚገልጽ እና ማነነቱን የሚያሳይ ትረካ ነበረው። ይሁን እንጂ ታገል በአቁዋሙ አልጸናም። ለተወሰኑ አመታቶች ማህበራዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ሲጽፍ ቆይቶ በሁዋላም አስቂኝ እና ለየት ያሉ ጉዳዮችን የያዙ ተንቀሳቃሽ እና ቁዋሚ ምስሎችን ከድምጽ ጋር እያዋሃደ በሲዲ እያወጣ መሸጥ ጀመረ። ለጠቀ እና የአዲስ አበባ መስተዳደር የቴሌቪዥን ፕሮግራም ሲጀምር ታገል እነዚያን ምስል ከድምጽ ጋር እያወዳጀ የሚሰራቸውን ቪዲዮዎች ማቅረቡን ቀጠለ። በነዚህ ቪዲዮዎች ውስጥ ታዲያ ታገል አዘውትሮ ታዋቂ በተለይም ሃብት ያላቸውን ሰዎች እንደ አትሌቶች ያሉትን አወዳሽ እና አሞጋሽ ስራዎች ላይ ማተኮሩን አዘወተረ። ታዲያ እንዳውም ከሃይሌ ገብረ ስላሴ እና ከደራርቱ…ከጥሩነሽ እና ከሌሎቹም የገንዘብ ስጦታ ከጅሎ የሰራቸው ስራዎች እንዳሰበው ስኬታማ ሳያደርጉት እንዲያውም የሚከፈለኝ ክፍያ በቂ አይደለም በሚል የክፍያ እድገት ከአዲስ አበባ መስተዳደር ቲቪ ሃላፊዎች ጋር ሳይግባባ ቀርቶ ከስራው ተሰናበተ።
እንግዲህ ግጥም አሳትሞ በቂ ገቢ ማግኘት ለታገል አስቸጋሪ ሆነበት መቆየት ብቻም አይደለም የልጁ እናት ላይ የፈጸመው ያማያዳግም በደል ታገል ህይወት ላይ ጥላውን አጠላበት። ከዚህ በሁዋላ ነበረ እንግዲህ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ በተዋቀረው የኢቲቪ መዝናኛ ፕሮግራም ውስጥ እግሩን ለማስገባት የ አቶ በረከት ስምኦንን ደጅ መጥናት የጀመረው። የሆነው ሆኖ ግን ታገል ያሰበው ሳይሆን ያላሰበው የነዋይ በረከት በበረከት ስምኦን በኩል የፈሰሰለት ወቅቱም መለስ ዜናዊ ላይመለስ በሞት ያሸለበበት ነበረ እና እነሆ የታገልን አፍቃሪ ነዋይነት ግልጽ አድርጎ ያሳየው ስሙን መጥራት የማልፈልገው አዲስ መጽሁፉ ላይ የመጽሃፉን መታሰቢያነት ለ መለስ ዜናዊ ልጆች እንዲሰጥ ሆኖዋል። እንዲያውም በዚህ ጉዳይ የቁም ነገር ዘጋቢ ባቀረበችለት ጥያቄ መሰረት ሲመልስ አባታቸው ጊዜውን ሙሉ ላሃገሩ በመስጠት ለልጆቹ ጊዜ ሳይሰጥ በሞት ለተለየው አባት ልጆች ለመለስ ልጆች የመጽሃፉን መታሰቢያነት መስጠቱን በኩራት ተናግሮዋል።
እንግዲህ ይህንን ማንም ያስበው መለስ ዜናዊ ለልጆቹ ፍቅር ሳይሰጥ ያለፈበት ለ እትዮጲያውያን የሰራው እኔ የማውቀው ዘጎችን እርስ በ እርስ እንዲፋጁ እና እንዲባሉ እንዲከፋፈሉ ከማድረግ በላይ በራሱ በመለስ ዜናዊ የቀጥታ ትዕዛዝ የተገደሉት የምርጫ 97 ሰለባዎችን የጨረሱበት ሁኔታ ነው መለስን ጊዜ አጥተው ለልጆቻቸው ፍቅር እንዲሰጡ ጊዜያቸውን ከ ልጆቻቸው ጋር እንዳያሳልፉ ያላደረጋቸው። ታገል እንግዲህ ከዚህ ሁኔታ ስር ነው ያደፈጠው። ይህ ብቻም አይደለም ታገል በፌስ ቡክም ዙሪያ መረን የለቀቀ አስተያየቱን ሰጥቶዋል የፌስ ቡክ ማህበራዊ ድረ ገጽ ተጠቃሚዎችን አብጠልጥሎ ስድ ስድቦችን ተጠቅሞ ተሳድቦዋል። ከዚህ በላይ “ጌታዋን የተማመነች በግ ላትዋን ደጅ ታሳድራለች” የሚለውን የሚያስተርት ምን ይገኝ ይሆን ? አይ ታገል እንጭጩ! አይ ታገል መረኑ! ሌላም አለ ሃብታሞችን በመጽሃፉ የምስጋና ገጽ ውስጥ ማመስገኑን መግለጹን አስመልክቶ ቁም ነገር ላይ ሲጠየቅ “ደሃን የማመሰግንበት ምክንያት የለኝም” በማለት ለድሃው የመጽሃፉ አንባቢም ሆነ በዚያ የቲቪ ኩመካው የሚያደንቀውን ደሃ ህዝብ ማስታወስ አልፈለገም። ስለዚህ የተመሰገኑት የሃብታም ምልክቶች ደግሞ መለስ ዜናዊ እና በረከት ስምኦን ናቸው። እንግዲ ማንም ማስተዋል ይችላል ይህ ልጅ ምን ማለት እንደፈለገ ይበልጥ መገንዘብ የሚቻለው ፌስ ቡክን የመጸዳጃ ቤት ግድግዳ እንደሆነ ሁሉ በማመላከት ነው ታገል የተናገረው። እንግዲ ፌስ ቡክን የመሰለ የነጻነት ወንጌል የሚሰበክበትን ማህበራዊ ድረ-ገጽ አብዮተኛዎቹንም ጭምር አንቁዋሾ ገልጾዋቸዋል። እኔ ደግሞ ግብጽን ያየ…ቱኒዚያን የተመለከተ…የሊቢያን መጨረሻ ያስተዋለ ለታገል የሚሰጠው ምላሽ ምን እንደሆነ መገመት አያዳግትም። ደግሞም የመናገር የመጻፍ የመሰብሰብ እና የመደራጀት ነጻነትን ከሚያፍኑ ሃብታሞች ብሎ ከገለጻቸው ሰዎች የተጠጋው ታገል መልዕክቱ ግልጽ ነው። በመጨረሻም የምለው በፌስ ቡክ ድምጻቸውን የሚያሰሙ የሚታገሉ አብዮተኛዎች ራሳቸውን መከላከል ካልቻሉ ሌኒን እንዳለው ራሱን መከላከል የማይችል አብዮት እርባና የለውም እና በአንድ ረብ የለሽ ግለሰብ የተሰደባችሁ አብዮተኛ ሳተናዎች ራሳችሁን ተከላከሉ እላለሁ። ከማን ካላችሁኝ ኢሃዴግ ካምፕ ውስጥ ተወልዶ ካደገው አውሬ ብያለሁ። አበቃሁ ሰላም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ክቡር ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ምን እያስተማሩን ነው?

11 Comments

  1. This is simply character assassination………..
    Mr. writer, you are mathimatically idiot
    I JUST GEOMETRICALLY INCREASE MY LOVE TO TAGEL SEYIFU

  2. @Teshome….Squarely Tagelin batakebrewu neber yemigermegn. ye mgbar abatih eko newu…behodamnetih, betelalakinetih, bemerzaminetih, behilina-bisnetih, bedinkurnah esun timeslaleh. Thefore, it should come as no surprise to see you defending this opportunist poet named Tagel. birille erasoch nachuhu huletachihum.

  3. It seems for me not fair on the person. Gotegninet yibikan!!! mandelam hone ghandin eyachew tilewut yalefutin agere. ke yihadig yebase agezaz tilew le agerachew selamin democracina limatin asirekebu. ende ante ayinet chifin tilacha lay temerikuzew siwagu yeneberut yehadigochin eyachew democracy enametalen bilew eshi bilen sef sinil nakun egna bicha nen yeminakew alun wendimochachin. Chifin tilacha ena chifin fikir yetim ayaderisenim hulachinim wendimina ehit nen. hulachinim le agerachin enasibalen gin chigiru egna yasebinew bicha sinil new. le sew eko tiliku ye netsanet telat sew new. be mejemeriya ke respect eninesa asitesaseb eko ye evolution guday new ye personality guday adelem ……….
    best of luck my people!!!

  4. Dear Tagel,

    I know you and your family in Jimma. your father was accused of and jailed for years by EPRDF for the red terror crimes he and his friends committed in jimma when he was one of the jimma municipality heads. So we don’t be surprised if Tagel follows the foot prints of his dad and advocates for facists. He is opportunist and still running after bereket to get coins for his daily life. Tagel shame on you!!

  5. Tagel mejemeriawns man neberna new?
    Weyanien degefe aldegefe min yametal? Esu Abebe Gelaw new endi? Enkef lenkef bidegagef…….

  6. sile ye press freedom eyaweru hasabune be netsanet yegeletse sewen mesdeb mine yelutale ende ene ende ene hodam malet hasabune be netsanet yegeletse sewen yemisadeb endezih aynetu tsehafi newe

  7. Hodam hule yemitayewu hodu becha newu yetem ayedersem bereketim tetekmobet sebekaw yewerewurewal. betam yemigermewu Melse lelegochu gize yatawu le ageru selefa mebalu newu ager seyatefana hezbin endet endmigel seyaselase yatawun gize belele neger memesel ye awagun bejoro yehonal yesentu leg degri yezo yale sera senkeratet yeminorewu bema gef agezaz newu ahuns behon yesu jelewoch mechi tewuna wedebasewu azekt ageritun eyeketetu ayedel ende enden Teshome ena Tagel ayenetochu banda wonafochi hule yemidela meseloachewu le enesu seyachaferu bemecheresha yetarik atela honewu mekretachewu ayekerem ewunetu endehon be ewunet tenagarewoch benante bekul yegeletalna bertu.

  8. Pls guys grow up asifiten enasib …. mesedadeb tiru negere adelem … be mejemeriya yerasachinin hilina keza demo yesedebinewun sew yigodal …….be sekene menifes enasib kalihonem minim aninager…….

  9. How far we can go with out respecting someone’s idea? Why do you need every body to follow your only vision? He has a right to be what he want to be. you need to learn how to win his idea not his attitude. Rather it is better to show us what idea you bring to fight the governor body. Tagel is just one person and you are too.you guys may have different angle of view to see the EPRDF. you have a right to oppose as well he has a right to support, so what is your problem?

  10. ለ ዘ-ሐበሻ
    First and for most, Tagel is a talented writer. Everyone was applauding and praising him for his work UNTIL he wrote something positive about EPRDF or Meles. I don’t think this is a fair judgement! Everyone is entitled to their opinion and they shouldn’t be crucified and discredited for their previous work. Tagel didn’t write not just about rich people…he wrote about social issues, heroes and other entertaining issues. Second, if our argument is that ‘Meles is sowing the seeds of hatred among us’, then, why are we helping him to succeed by hating each other? እሳትን በእሳት ማጥፋት ይቻላልን? In my opinion, criticizing his view on Meles is fair. BUT, tormenting all his previous works and his professional career is just out of line! As you might have guessed, I am a big Tagel fan!

Comments are closed.