“በኦሮሚያ ክልል የተፈፀመውን ግፍ፣ አማራ ፈፅሞት ቢሆን ኖሮ ስንት አኖሌ ሀውልት ይሰራ ነበር?” – አቶ ዮሐንስ ቧያለው

298918269 2710874359046386 5788556753264331852 n
በኢትዮጵያ 3 አይነት ዜጋ አለ። አማራ በአሁኑ ሰዓት 3ኛ ደረጃ ዜጋ ነው። በወያኔ ጊዜ 2ኛ ደረጃ ዜጋ ነበር። አንደኛ ደረጃ ዜጋው ጊዜው የእኛ ነው የሚለው አካል ነው። ሁለተኛ ደረጃ ዜጋው ደግሞ ሌላው ብሄር ነው። በሶስተኛ ደረጃ የአማራ ህዝብ ነው። አሁን ላይ የአማራ ህዝብ በኢትዮጵያ የሚኖረው ከሱዳን ስደተኞች፣ ከኤርትራ ስደተኞች፣ ከሶሪያና ከየመን ስደተኞች በታች ነው።
በጦርነት ጊዜ ያልተባለ፣ ከጦርነቱ በሗላም ያልተነሳ … ድንገት ሰሞኑን ፋኖ ከመከላከያ ላይ ጥቁር ክላሽ ቀማ የሚለው እንዴት መጣ? አትሞኙ፣ ይሄ አዲስ የአማራ ጥላቻ ትርክት እየተፈጠረልን ነው። ነባሩ ትርክት አልበቃቸው ስላለ ነው። የጥቁር ክላሽ ትርክት የመጣው፣ የኦሮሚያ ብልፅግና ተረኛ አመራሮችን ጥቁር ታሪክ ለመሸፋፈን ነው። በእነዚህ አመራሮች መሪነት አማራ ታርዷል። የ15 ቀን ህፃን ከእነ እናቷ ተገድላለች። ታዳጊ ህፃን ሁለተኛ አማራ አልሆንም ብላለች። ጥቁር ታሪካቸው ተዘርዝሮ አያልቅም።
በኦሮሚያ ክልል የተፈፀመው ግፍ፣ አማራ ፈፅሞት ቢሆን ምን ይፈጠራል? ኦሮሚያ ውስጥ የታረዱትን ያህል፣ አማራ ውስጥ ሌላ ብሄር ታርዶ ቢሆን ምን ሊፈጠር ይችላል? ብላችሁ አስቡት። በበቀል አፀፋ ኢትዮጵያ የደም ጎርፍ ትሆን ነበር። ሀገር ሙሉ በሙሉ ይፈርስ ነበር። ስንት አኖሌ ሀውልት ይሰራ ነበር።
(አቶ ዮሐንስ ቧያለው – ፋኖነት በሚለው የመፅሐፍ ምርቃት ላይ የተናገረው)
ተጨማሪ ያንብቡ:  ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 8 - ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች

Leave a Reply

Your email address will not be published.