በሀገራችን የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መዳበር አስፈላጊ መሆኑን በጽኑ ያምናል – ኢዜማ

emaለዚህ ሥርዓት መዳበር ዋና ሚና ከሚጫወቱት ተቋማት መካከል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተጠቃሽ ናቸው። እነዚህ ፓርቲዎች የሀገሪቱን ሕጎች አክብረው በሰላማዊ መንገድ እስከተንቀሳቀሱ ድረስ ማንም አካል በሐይል እንቅስቃሴያቸውን ሊያስቆም አይገባም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተመለከትነው እንዳለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ጉባዔዎቻቸውን እንዳያደርጉ እየተከለከሉ ይገኛሉ። ለአብነትም የካቲት 26/2015 ዓ.ም እናት ፓርቲ እንዲሁም በዛሬው ዕለት መጋቢት 03/2015 ዓ.ም የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ጉባኤ እንዳያደርጉ ክልከላ ተደርጎባቸዋል።

ይኽ ተግባር የመድብለ ፓርቲ ሥርዓትን ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት የሚያከስም ዓይን ያወጣ ህገ ወጥ ተግባር በመሆኑ የመንግስትን ድርጊት በጽኑ እናወግዛለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሠል ድርጊቶችን ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት የምንረዳ ቢሆንም የችግሩን ልክ በሚመጥን መልኩ ሐላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን።

በተጨማሪም በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት የፀጥታ ሐይሎች በሕግ ከተሰጣቸው ስልጣን በመተላለፍ እንዲህ አይነት ሕገወጥ ድርጊቶችን ባለመፈፀም ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መዳበር ገለልተኛ ተቋምነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ እናቀርባለን።

እንዲህ አይነት ሕገወጥ ተግባር ሲፈጸም ምንም እንዳልተፈጠረ የምትመለከቱ የመንግስት አካላት እና የሕዝብ መገናኛ ብዙሃን በዝምታ የድርጊቱ ተባባሪ መሆናችሁን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሕዝብ ግንኙነት

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለዶ/ር አብይና ብልጽግና ፓርቲ እጅግ አሰቸኳይ የዜጎች እልቂት መፍትሄ መልክት

3 Comments

  1. ምንም አያምርባችሁም ብርሀኑ በግሉ ይስጥ። ከቀስተ ደመና እስከ ኢዜማ ስራችሁ ሁሉ ጠለፋ ነው። አንዱ አለም አራጌ ላይ ፈርደህ እስክንድር ላይ አላግጠህ ህዝብ ይረሳዋል ብለህ አታስብ። ባልደራስ መሰብሰብ ተከልክሉዋል እናንተ ቤተመንግስት ትጋበዛላችሁ። በል እንግዲህ ያንተ ፕሮፌሰር ከገባህበት ማጥ ያውጣህ አቅሙ ካለው።

  2. I am sorry to say but I must say that you guys have already damaged if not destroyed the very essence and value of multi-party politics when you are stupidly and painfully failed the people 4+ years ago by becoming the very self-disgraced under dogs or the mere barking dogs of Abiy’s deadly ruling circle!
    It is from this very tragic political behavior of your own that it is quite fair to say that whatever you may claim and cry about a multi-party-political system remains just good for nothing way of thinking!
    Believe or not, your political path you chose is an absolute stupidly as far as the continuation of the same deadly political system that has caused and keep causing unprecedented crisis in the very political history of the counter is concerned!
    By the way, is it not an open secret that you are part and parcel of the deadly political orchestration of the so-called Prosperity Party? Absolutely it is!
    Don’t you guys have any sense of shame if not very disturbing moral decay when you keep extremely nonsensical political statement (meglecha) years and after years?
    Why do you cry about the untold sufferings and killings of innocent citizens whereas you are parts and parcels of the very horrifying suppression and killings machines of the ethno-politics merchants of the so-called Prosperity Party?
    If you are serious enough about the very question of how and when to get out of the very unprecedented level of national crisis because of the merciless merchants of ethnic politics, it is necessary and urgent for you to get out from the very tragic partnership you continue muddling in!

  3. After you aid, abet and assist PP in illegally extending its term, committing ethnic cleansing, geocide and plunder,
    After you cover up PP’s crimes against humanity and Ethiopians,
    After you paralyze Ethiopians with false propaganda so they cannot unite in their fight against PP,
    you have the nerve, audacity and condescension to come out with pretentious statements such as these?

Leave a Reply

Your email address will not be published.