ተዋናይት ሜላት ዳዊት ከእስር እንድትፍታ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ቢሰጥም ፖሊስ ይግባኝ ጠየቀ ! ( ይድነቃቸው ከበደ )May 31, 2023ሰብአዊ መብትየፊልም ዳይሬክተር እና ተዋናይት ሜላት ዳዊት ፤ በዛሬው ዕለት ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓ.ም. አስሯት የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ፣ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት እንድትቀርብ አድርጓል ።ፖሊስ ለባለፉት 7 ቀናት ፍርድ ቤት በሰጠው የምርመራ ቀናት ፣ ከዚህ ቀደም ይቀሩኛል የሚለውን የምርመራ ሂደት አጠናቆ እንዲቀርብ ጊዜ የተሰጠው ቢሆንም ፣ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ 14 የምርምር ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል ።ሆኖም ግን ፤ ፍርድ ቤቱ ከዚህ ቀደም ለፖሊስ የተሰጠው የምርመራ ቀናት በቂ በመሆኑ ፣ እንዲሁም ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው ጊዜ የተለየ የምርመራ ሥራ አልተሰራም በማለት ፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፣የፊልም ዳይሬክተር እና ተዋናይት ሜላት ዳዊት በ5 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ጉዳዩን ከእስር ተፈታ እንድትከታተል ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል ።ጠዋት በዋለው ችሎት ፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፤ ተዋናይት ሜላት ዳዊት በ5 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ የሰጠውን ትዕዛዝ በመቃወም ፤ ፖሊስ ለከፍተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሰዓት በዋለው ችሎት ይግባኝ ጠይቋል ።ይግባኙን የተመለከው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ፤ በታችኛው ፍ/ቤት የተሰጠውን ትዕዛዝ መርምሬ ” ውሳኔ የምሰጠው ፤ ነገ ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ 8 ፡00 ሰዓት ነው ” ብሏል ።All reactions:259259ተጨማሪ ያንብቡ: ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ራያ የትግራይ አካል ሆኖ አያውቅምየእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ[email protected] በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!Leave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ