አማራው በዘሩና በማንነቱ እየተገደለ ያለው በአብይ አህመድ እና በሽመለስ አብዲሳ ቀትተኛ ትዛዝ ነው

May be an image of 1 person and sunglasses“በዘሩና በማንነቱ እየተገደለ ያለው የክልሉ ፕሬዝደንትና በኦሮምያ ብልፅግና ቢሮ ኃላፊዎችና አመራሮች ናቸው እንጂ ሸኔዎች አይደሉም። በእነሱ የተቀናባበሩ ሸኔዎች ናቸው ግድያውን እየፈፀሙ ያሉት። ነገ ፀፀት እንዳይኖርብኝ ይቺን ልናገር። yes! እውነቱ ይሄ ነው።
ሁለት አይነት ሸኔ ነው ያለው። እውነተኛው ሸኔ እና ሳቦታጅ ሸኔ ነው ያለው። ሳቦታጁ ሸኔ የሚመራው በኦሮምያ ክልል አመራር ነው። የኦሮምያ ክልል አመራርና የኦሮምያ ክልል ብልፅግና ቢሮ ከእነ አማራሮቻቸው ከነካቢኔዎቻቸው ካልተፈረካከሱ በቀር በጭራብ ሞት ግድያ በኦሮምያ ሊቆም አይችልም።
ይቺን ተነጋሬ ነገ ጠዋት ልሙት። ፀፀት የለብኝም እኔ። ስለምናውቅ ነው የምንናገረው። ስለምናውቅ…. የሰው ነፍስ ያነገበግበናል…. ቋቅ ብሎናል….ቋቅ ብሎናል። መግለጫ ሰልችቶናል። የሀዘን መግለጫ ቋቅ ብሎናል እኛ አንፈልግም!
የሀዘን መግለጫ ድንኳን ማሳመሪያ ልንሆንን አይደለም ወደ ኢትዮጵያ የመጣነው። ንፁሃንን ከግድያና ከስርቆት ለማትረፍ ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣነው። ማንንም ለማጀገን፣ ማንንም ለማጥፋት አይደለም። በፍፁም። የብሄር ብሄረሰብ እልቂት ሁሉ ነገር ተቀምሞ እየተሰራጩ ያለው ከኦሮምያ ክልል ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት እና ከኦሮምያ ክልል ብልፅግና ቢሮ ነው። እዚያ ላይ ያሉ አመራር እና አሰራሮች ሁሉ ከነካቢኔው ካልተገልበጡ በሙሉ ሞት መቼም ሊቆም አይችልም ቃል ለምድር ለሰማይ!!” :-አንጋሳ ኢብራሄም – የምክር ቤት አባል።
የንፁሃን ደም ይጮሃል!!
ተጨማሪ ያንብቡ:  " ሽርፍራፊ ስልጣን ለግለሰብ ኢጎ እና ጥቅማጥቅም እንደሆነ እንጂ ለህዝብ የተለየ አማራጭ ሃሳብ እንዲያገኝ አያደርግም ! " ተክሌ በቀለ

Leave a Reply

Your email address will not be published.