ጨው ሆይ! ድልህ አዋዜን ባሳማርክ፣ ቀይ አልጫውን ባጣፈጥክ፣ በጥርስ መንጋጋ ታኝከህ፣ በምላስ ጪልፋ ተላውሰህ፣ በማንቁርት ክርን ተገፍተህ፣ የጉረሮን ቦይ ተሻግረህ፣ በከርስ ወፍጮ ተፈጨህ፣ በእባብ አንጀትም ተበላህ፡፡ ምግቡን በአሻቦ ጣዕም አርገህ፣ ውሀንም በአንካር አጣፍጠህ፣ የተራበውን በመገብክ፣ የተጠማውን ባጠጣህ፣ የኮሰመነ ባፋፋህ፣ የመነመነ ባወፈርክ፣ ደም ግፊት አምጪ እያሉ፣ ይሉኝታ ቢሶች ኮነኑህ፡፡ ሙያ የለሹን ሰው ባረክ፣ የመብል ጣዕምን ባስተማርክ፣ ውሻ እማይነካውን ምግብ፣ ጣት አስቆርጣሚ ባደረክ፣ ሕዝብን ተንሰሳ በለየህ፣ ተሳር ጋጪነት ባወጣህ፣ እጅህ እንደ አማራ ሕዝብ፣ አመድ የሚያፍስ ሆኖብህ፣ “ለራስህ ስትል ጣፋጭ ሁን፣ አለዚያ ድንጋይ ነህ” አሉህ፡፡ እንግዲህ ተልድምህ ተማር፣ መጣፈጥ መጣም ይቅርብህ፣ ዓለም ከንቱ እንደሆነች፣ እናት ደግ እንደማትወድ ይግባህ፡፡ በልተው እንዳያጠፉህ፣ ጠጥተው እንዳይጨርሱህ፣ አትብሉኝ
The post ጨው ለራስህ ስትል አትጣፍጥ! – በላይነህ አባተ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>እውነትን መወንጀል ዛሬ አልተጀመረም፣ ጥንት የነበረ ነው ሲፈጠር አዳምም፣ እግር አልባ ሳይሆን በእርግማን እባብም፡፡ እውነት የሚያሳድድ ከርሳም ስለበዛ፣ ለቅጣት ለትምህርት ጥፋት ውሀ መጣ፡፡ ጎርፉ ነጎድጓዱም ስላስተማረው፣ ከሀዲ ስግብግብ ምድሩን ስሞላው፣ ሰዶም ገሞራውን በእሳት አመደየው፡፡ በቃል በምልክት ሰው ስላልተማረ፣ በአካል ለማስተማር መለኮት ወረደ፡፡ መለኮት እውነትን መሆኑን የካዱ፣ ባንዳ ፈሪሳውያን ማርያምን የከዱ፣ ለሄድሮስ አቃጥረው ማሳደድ ጀመሩ፣ በሁለት ዓመቱ አንገት ሊያሳርዱ፡፡ ለኃጥአን የመጣ ደርሶ ለፃድቁ፣ በሄሮድስ ቢላዋ ሺዎቹ ታርዱ፡፡ በእናት ጀርባ ታዝሎ በርሃ ቢገባም፣ እውነትን ማሳደድ ባንዳው አላቆመም፡፡ የኦሪትን ሕጎች እያነበነቡ፣ አንዷንም በግብር ጭራሽ ሳያውሉ፣ ዘርፈው እየበሉ እያመነዘሩ፣ ሰው እያሳረዱ ሲቀጥፉ እየዋሉ፣ “የሙሴን ሕግ ጥሷል!” እያሉ ከሰሱ፡፡ ምስክር ዳኛዎች እራሳቸው ሆነው፣ ባንዳዎች ከሰሱት
The post ባንዳ ፋኖን እሰር እስክትሆን አፈር! has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>እኔዎች (እኔያት) አንዱ እኔ ሲጠራኝ አንዱ እኔ ሲልከኝ ሌላው እኔ ሲጥለኝ አንዱ እኔ ሲያነሳኝ፣ አንዱ ወደ ግራ ያአንዱ ባለጋራ አንዱ ወደ ደጅ የሌላው ወዳጅ፣ ሌላኛው ወደ ቀኝ ሌሎቹን እንዲዳኝ አንደኛው ወደ ታች ለራሱ ሊያመቻች፣ አንዱ ወደ ላይ ሊነካ ሰማይ አንደኛው ወደ ፊት ሌሎቹ እንዳይቀድሙት አንዱ ወደ ኋላ ሊያጣራ ሊያብላላ፤ አቤት የእኔ መዓት የራሴ ብዛቱ ለየቱ እንቢ ብዬ ልታዘዝ ለየቱ? እኒህ ሁሉ እኔዎች ውስጤ ተከምረው ሁሌ እየተጣሉ አልስማማ ብለው አንድ እኔ ባተለ ፍዳውን ቆጠረ ሌላው ኔ ደስ ብሎት ተኝቶ እያደረ። በላቸው ገላሁን (ነሓሴ 1998) (USA)
The post እኔዎች (እኔያት) – በላቸው ገላሁን has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>በደኖና ዝዋይ፣ ቡራዩና ቄለም ኦነግ ያፈሰሰው ያማራ ጥቁር ደም ውሻ ልሶት ቀርቶ እንደሌለው ወንድም እንዳይፋረድህ በወዲያኛው ዓለም፣ አማራ ጦር አንሳ ኦሮሙማን ግጠም በሂወትህ ቆርጠህ ሞት ሽረት ተፋለም፡፡ ደም በደም ካልጠራ ስለሚሆን መርገም ባፈሰሰው ደም ልክ አፍስስ የኦነግ ደም፡፡ እውነትም ከሆንክ የጀግና ልጅ፣ እየተሰኘህ ደም አዋራጅ እንዳትረገም ባንተው ወላጅ ፎክረህ ተነስ ፈጽም ግዳጅ፡፡ ሳ(ት)ጠይቅ ካሳ ወይ አማላጅ የወንድምህን ገዳይ አራጅ ተፋልመህ ማርከህ አስረህ በፍንጅ ገድለህ እየጣልክ እራሱ ደጅ የእጁን ስጠው በራስህ እጅ፡፡ “የማን ቤት ፈረሶ የማን ሊበጅ ያውሬ መውለጃ ይሆናል እንጅ ሳለ ደመላሽ የጀግና ልጅ፡፡” መስፍን አረጋ [email protected]
The post ደመላሽ – መስፍን አረጋ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>ወገኑ ተወስዶ ሲታረድ በካራ፤ ድምጡን ጥፍት አርጎ የሚውጥ ሙዳ፣ እምብርት ማተብ የለው ሰው መሳይ አሳማ፡፡ ዓይኑ እያስተዋለ ጆሮው እየሰማ፣ ዘመድ ተሰውቶ ጥብስ ወጥ ሲሰራ፣ አፍንጫው አሽትቶ ለኻጩ እየወጣ፣ አፉን ተምግብ ተክሎ ያገኛል ደስታ፣ ደመነፍስም ፍቆ የዛሬው አሳማ! የዘመኑ አሳማ እጅጉን እርኩስ ነው፣ እንኳን የወንድሙ ሥጋ ቅፍፍ ሊለው፣ የራሱም ፍሪንባ ተቆርጦ ቢሰጠው፣ ተስገብግቦ ሳስቶ እሚዘነችር ነው፡፡ መኖ ተጣሉለት ወደ አፍ የሚገባ፣ ዓይኖቹ እማያዩ ጆሮው የማይሰማ፣ ተፊቱ ደም ቢፈስ ቢከመር ሬሳ፣ ጩኸት ቢበረክት ወገን ቢያፈስ እንባ፡፡ ሊያርዱና ሊበሉ ለነገ ሲያደልቡት፣ ወንድም እህቶቹን አርደው ሲመግቡት፣ ምንም ሳያቅማማ ዝም ብሎ የሚውጥ፣ እንደ ጉንዳን ፈልቷል ተአገሬ ምድር ውስጥ፡፡ እንኳን ቅዱስ ፍጡር እርኩሱን አሳማ፣ ተጭራቅ ታራጆች
The post አሳማ! – በላይነህ አባተ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>መከራን እንደመጋፈጥ፣ ፈርቶ የሚፈረጥጥ ይጠብቀዋል ቀውጥ፣ ይበልጥ የሚሰቀጥጥ፡፡ ጣጥሎ በመሮጥ፣ እየመሰለው የሚያመልጥ ይገባል ብሎ ቀጥ፣ ከሳት ወጥቶ ረመጥ፡፡ ጭራቅ አሕመድ ጦርነት እገጥማለሁ ያለው ከእስክንድር ጋር ብቻ ሳይሆን እስክንድርን ከመሰሉ ሁሉ ጋር ነው፡፡ በጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ግዛት ውስጥ ኦነጋዊ ያልሆነ ሁሉ ጊዜው ደርሶ በሜንጫ ተቆራርጦ በጭራቁ እስከሚበላ ድረስ መኖር የሚችለው የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ ጉዞ ለይስሙላ ቢቃወምም በተግባር ግን የማያደናቅፍ እስከሆነ ድረስ ብቻ ነው፡፡ የጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ጉዞ ደግሞ መዳረሻው አማራን ድምማጡን ማጥፋት ነው፡፡ ስለዚህም ጭራቅ አሕመድ ለአማራ ሕዝብ የሰጠው ምርጫ ሁለትና ሁለት ብቻ ነው፡፡ አንደኛው ምርጫ (ምርጫ ከተባለ) ተራ በተራ እየታረደ በጭራቁ ተበልቶ እስከሚያልቅ ድረስ የጭራቁን ጭራቃዊ አገዛዝ አሜን ብሎ ተቀብሎ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ ነው፡፡ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ የጭራቁን
The post ጦርነት እገጥማለሁ ካለ ጋር ያለው አማራጭ መግጠም ብቻ ነው – መስፍን አረጋ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>እንደ ዋላ ውሀ እደጠማት እንደራባት ጥም እንደያዛት የሚያሳብቀው ገላዋ ጎስቋላ ነው ስጋዋ ይህቺ እማማ….. አዲስ አቁማዳ ተሸክማ አየኋት ማህሌት ቆማ አዳዲስ ዜማ ስታዜም ስትደረድር ስትገጥም አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅልኝ የወይን አረግ ጥመቅልኝ እባክህ ውዴ …. እንጀራዬን ልጋግረው ላስፋ ፍለቅ እባክህ የኔ ተስፋ ዳኘው ገበታየን ጎብኘው ቃል ኪዳኔን ብይኔን ክፈት ደጁን የማይ መቅጃየን የምንጩን ላጠጣ አብራኬን ላርካ ልዘምርልህ እጄን እንካ የምስጋና ነዶ ይዤ እቅፍ ሙሉ አበባ አስይዤ ከከፍታው ተራራ ላይ አወጣለሁ ስእለቴን እከፍላለሁ እያለች ማህሌት ይዛለችና ክፈትላት እባክህ ራራና አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅላት ቆማለችና ተለመናት እባክህን ፍለቅላት ተገለጥማ እሺ በላት እባክህን እባክህን እባክህን እባክህን እባክህን ብዬ ስልህ? ሀምሌ፣ 2014 Geletaw Zeleke
The post አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ! has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>ጎህ ሳይቀድ ማለዳ የአማሮች መርዶ ጎህ ሳይቀድ ማለዳ የትግራዋይ መርዶ ደግሞ ማልዶ ማልዶ የኦሮሞ መርዶ ደግሞ ማልዶ ማልዶ የኮንሶዎች መርዶ ደግሞ ማልዶ ማልዶ ያገሬ ልጅ መርዶ አዘን ደረበባት ኢትዮጵያ አይኗ ጠፋ ልቧ ተሰበረ ውሰጥ አንጀቷ ከፋ በቃ በይ እባክሽ ፀሀይ ውጪ ውጪ የመልካሙን ዜና እቅፍ ነዶ አምጪ ጎህ ቅደጂ ፀሀይ አ’ዋፍት አሰማሪ የደስታን ዜና የሰላም አዝማሪ ማልዶ መርዶ ቀርቶ የሀሴት ሆኖለት አበሻ በሙሉ እንጀራ ይውጣለት….. ሰላም ይሁንለት…. ደሰታ ይሁንለት….. እባክሽን ፀሀይ ዛሬ ለታ ውጪ እባክሸን ፀሀይ እባክሽ እባከሸ እባክሽን ሰልሽ? ሀምሌ 7 ቀን 2014 ገለታው ዘለቀ
The post ፀሀይ ውጪ ውጪ! – ገለታው ዘለቀ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>እንዲህ ሹክ ይለኛል የምኞት ፋብሪካ አቢይ አህመድ አሊ ሳይሞት ሳይነካ ቪቫ ሲሪ ላንካ! የካድሬን ኩይሳ የተቦረቦረን ያለቀን ተበልቶ ሕዝቡ እንደ ንብ ተምሞ ይደርምሰው ገብቶ ከውቅያኖስ ማዶ ላሰማችው ፊሽካ ቪቫ ሲሪ ላንካ አቢይ አህመድ አሊ ሳይሞት ሳይነካ የሌላ ደም ሳይፈስ መተከል ወለጋ ኢትዮጵያ ሳትከፍል ተጨማሪ ዋጋ በሩን ክፈቱለት ወደሚያሻው ይንካ ቪቫ ሲሪ ላንካ! የጠላትን ሴራ ሁሉም ይወቅ ይንቃ የንጹሐኑ ደም የጎረፈው ይብቃ ወታደሩ ይባል ማሎ ሳቂ ሳንቃ* ለሁሉም በእኩል ይዘርጋ ሰደቃ አንዴ ሳይቆረጥ አሥሬ ይለካ መድሓኒትም ቢሆን አይለፍ ከማንካ ሕዝብ እንጀራ ይጋግር የራሱን ሊጥ ያቡካ ቪቫ ሲሪ ላንካ! *ሳቂ ሳንቃ = በሩን ክፈት ሲሪ ላንካ = ሕዝብ መስዋእትነት ከፍሎ በሰላማዊ ማእበል መንግሥት
The post ቪቫ ሲሪ ላንካ! (ከአሁንገና ዓለማየሁ) has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>እስከመቼ ድረስ? ታዳሚውን በእንባ ያራጨ ድንቅ መልዕክት – ጦቢያ
The post እስከመቼ ድረስ? ታዳሚውን በእንባ ያራጨ ድንቅ መልዕክት – ጦቢያ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>አሻጋሪ ድልድይ ስትል የነበረው፣ መቀመቅ አስምጦ እየጨረሰህ ነው፡፡ ኩላሊትና ልብ ሳንባዬ ነው ያልከው፣ ምች ነቀርሳ ሆኖ ተምድር ሊያጠፋህ ነው፡፡ መብት ነፃነትህን ተእጅህ አዘርፈህ፣ ተእግር ብትደፋ እንዲመልስልህ፣ እንኳንስ ጭራቁ እግዜርም አይሰማህ፡፡ እርዳኝ እረዳለሁ ያለውን ዘንግተህ፣ አንጋጠህ ብትለምን እጅህን ዘርግተህ፣ እንደ አብያ በሬ አልምጠህ ተጋድመህ፣ አምላክ ጆሮው ጥጥ ነው ቅንጣትም አይሰማህ፡፡ ሙሴ ፈርኦንን በእምብርክክ ያስኬደው፣ ጀግንነቱን አይቶ መለኮት ሲረዳው፣ ባህሩን ሰንጥቆ መልሶ ሲሞላው፡፡ ዳዊት ጎልያድን ቀንድቦ የጣለው፣ ትጋት ልቡን አይቶ እግዜር ስላገዘው፡፡ ፋኖ መሶሎኒን ወገቡን የቀጨው፣ ማተብ ትግሉን አይቶ አምላክ ስለረዳው፡፡ ሁለት ልብ መሆን በአምላክ ቤት ፀያፍ ነው፣ መሐል እየሰፈርክ ጌታን አታስከፋው፣ ወይ ታራጅን አድን ወይ አራጁን እርዳው፡፡ ሕዝብ ሆይ ተመከር ልብህን
The post ነፃነትህ በእጅህ! (በላይነህ አባተ) has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>ጊምቢ ኤሎሄ ጊምቢ ቶሌ ትእዛዝ ወርዶ ከእገሌ ከሥልጣኑ ሉያ ሃሌ ለማይካድራ ጅኒ ቆሌ መስዋእት ሊቀርብ በንጹሕ ደም መቅጃ አኮሌ ዱበርቶኒ ፊ ኢጆሌ** ተጨፍጭፈው በወለጋ ጊምቢ ፎሌ ካንዲት ጎጆ አሥር ሞቶ ለኦነግ ዛር ተሠውቶ መሬት ጭረው እህል ዘርተው የሚኖሩ ከብት አርብተው የማይጽፉ ማያነቡ ጥያቂያቸው ወጥተው ወርደው ቤት ሲገቡ ሰላም ዋለ ቤተሰቡ? መጣ ቀረ ወይ ዝናቡ? ብቻ ሆኖ አራት ኪሎ የሚያውቃቸው አራት ኪሎን የማያውቁ እንደ ዶሮ ተከታትፈው እንደ አውሬ እየታነቁ እንዲያ ሲያልቁ ያስተዳድር የተባለው የመመከት ሥልጣን ያለው በከፈሉት ግብር ሰብቶ ባመረቱት ቀለብ ገዝፎ ካገር ጠላት ዲናር ልፎ ይሁዳኛ እየሳመ ሲሰጣቸው አሳልፎ ጊምቢ ሆና ጎልጎታቸው ቤትልሄምም ራሷ ጊምቢ መንደራቸው ድንገት ሆኖ የቀያፋው ትልቅ
The post ጊምቢ ኤሎሄ ጊምቢ ቶሌ (ከአሁንገና ዓለማየሁ) has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>ጠኔውም ቢገልህ ስጋም አንቆህ ብትሞት መዝግቦት ተጓዘ ታሪክ ያንተን ሐሞት ስትሳለቅ ነበር ትናንት በእስክንድር በአቋራጭ ቀዳድሞህ ቆሞልሃል ብድር። ስማኝ የሸገር ልጅ ኳስ ዳንኪራ ብርቁ ጊምቢ ቶሌ አይደለም እልቂቱ ፍጅቱ ያንተኑ ነገ ነው ያሳዩህ በሩቁ ንብረትህን ዘርፈው ቤትህን ሲያነዱ እትና እናትህን ልጅና ሚስትህን እንዴት እንደሚያርዱ ምን እንደሚመስል ያንተኑ ነገ ነው ያሳዩህ በሽንቁር ወለጋ ሩቅ መስሎህ የዋሁ ሸገሬ እንዳትደነቁር ከነግብራበሩ ነገ ብልጽግና ባንተ ደም ይዋኛል ግንፍሌ፣ ቡልቡላ፣ ቀጨኔ፣ ቀበና ጅቡ ርቆ ሄዷል ዛሬ ካዲሳባ ማን (man) ነው የሚበላው ነገ ያንተን ሬሳ ያካልህን ገራባ? ያ እንጂ ጥያቄው ያልመለሱት ገና በወለጋ ተውኔት የሸገርን እጣ ሲያሳይ ብልጽግና ሁሉን ጨርሶታል ነግ ያንተ ነው ተራው ገዳይህ ለታሪክ ተነግሮት አደራው ቃል እየጠበቀ ቆሟል በየሥፍራው ስምክም ተጽፎበት ተቀምጧል ገጀራው።
The post ስማኝ የሸገር ልጅ (ከአሁንገና ዓለማየሁ) has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>በዘር በቋንቋቸው በባትሪ በመብራት እየተፈለጉ፣ እንደ በግ እንደ ከበት ሰዎች ሲታረዱ፣ እግዜር ይጠይቃል ማን እንደነበሩ ስለቱን የያዙ፣ ትውልድ ያፋጥጣል እነማን አሳስረው ሕዝብ እንዳስጨረሱ፣ ታሪክ ይታዘባል ስንቶች ሆድ ለመምረግ አፍን እንደ ዘጉ፡፡ ግብር ገባሪዎች በደም በሥጋቸው እየተመረጡ፣ ተቤት ተእምነት ሥፍራ ለአውሬ ለጪራቆች ፍሪዳ ሲቀርቡ፣ ግብሩን የሚበሉት ፓርላማ ምንስቴር ወንጀል ሲደብቁ፣ እግዚአብሔር ይቆጣል ለዘር ማጥፋት ወንጀል ፍትህ በመጥፋቱ፣ ትውልድ ይዘግባል ምንስቴር ፓርላማ ማን እንደነበሩ፣ ታሪክም ያትማል ስንቶች ለከርሳቸው ሕዝብ እንደገበሩ፡፡ ለደም ለአጥንታቸው እየተፈለጉ በጎች ሲታረዱ፣ እረኞች “አባቶች” ይቺን ዓለም ወደው ዛሬም ዝም ሲሉ፣ እግዜር ልብ ያደርጋል በጥምጣም ካባቸው እንደሚያታልሉ፣ ትውልድ ያፋጥጣል በግን አሳልፈፈው ለምን እንደሰጡ፣ ታሪክም ይወቅሳል አቡነ ጴጥሮስን ስላልተከተሉ፡፡ ሕፃን ሴቶች
The post እግዜር ይጠይቃል! ትውልድ ይታዘባል! ታሪክ ይዘግባል! – በላይነህ አባተ has the Legal Rights of Ethio point ዘ-ሐበሻ (Zehabesha) የዕለቱ አብይ ዜና | ሰበር ዜና | አስተያየትና ትንታኔ | ዜና የኢትዮጵያ.
]]>