ጦርነት እገጥማለሁ ካለ ጋር ያለው አማራጭ መግጠም ብቻ ነው – መስፍን አረጋ

መከራን እንደመጋፈጥ፣ ፈርቶ የሚፈረጥጥ
ይጠብቀዋል ቀውጥ፣ ይበልጥ የሚሰቀጥጥ፡፡
ጣጥሎ በመሮጥ፣ እየመሰለው የሚያመልጥ
ይገባል ብሎ ቀጥ፣ ከሳት ወጥቶ ረመጥ፡፡

ጭራቅ አሕመድ ጦርነት እገጥማለሁ ያለው ከእስክንድር ጋር ብቻ ሳይሆን እስክንድርን ከመሰሉ ሁሉ ጋር ነው፡፡  በጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ግዛት ውስጥ ኦነጋዊ ያልሆነ ሁሉ ጊዜው ደርሶ በሜንጫ ተቆራርጦ በጭራቁ እስከሚበላ ድረስ መኖር የሚችለው የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ ጉዞ ለይስሙላ ቢቃወምም በተግባር ግን የማያደናቅፍ እስከሆነ ድረስ ብቻ ነው፡፡  የጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ጉዞ ደግሞ መዳረሻው አማራን ድምማጡን ማጥፋት ነው፡፡

ስለዚህም ጭራቅ አሕመድ ለአማራ ሕዝብ የሰጠው ምርጫ ሁለትና ሁለት ብቻ ነው፡፡  አንደኛው ምርጫ (ምርጫ ከተባለ) ተራ በተራ እየታረደ በጭራቁ ተበልቶ እስከሚያልቅ ድረስ የጭራቁን ጭራቃዊ አገዛዝ አሜን ብሎ ተቀብሎ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ ነው፡፡  ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ የጭራቁን ጦርነት ግጠሙኝ ገዲር (challenge) በጸጋ ተቀብሎ ከጭራቁ ጋር የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ወይ ጭራቁን ጨርቅ ማድረግ ወይም ደግሞ በጭራቁ መበላት ነው፡፡

አንደኛው ምርጫ ተዋርዶ ኑሮ ተዋርዶ የመሞት ምርጫ ስለሆነ የቱሪናፋ ምርጫ ነው፡፡  ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ተከብሮ የመኖር ወይም በክብር የመሞት ምርጫ ስለሆነ ያርበኛ ምርጫ ነው፡፡

ስለዚህም ተዋርዶ ኑሮ ተዋርዶ መሞትን የማይመርጥ አማራ ሁሉ አርበኛ ሁኖ፣ ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ ብሎ፣ የነ በላይ ዘለቀን ጦርና ጋሻ አንስቶ፣ የሞት ሽረት ትግል ለማድረግ ዱርቤቴ ማለት አለበት፡፡  ባትዋጋ እንኳን በል እንገፍ እንገፍ፣ ያባትህ ጋሻ ቱኻኑ ይርገፍ፡፡

 

በደኖና ዝዋይ፣ ቡራዩና ቄለም
ኦነግ ያፈሰሰው ያማራ ጥቁር ደም
ውሻ ልሶት ቀርቶ እንደሌለው ወንድም
እንዳይፋረድህ በወዲያኛው ዓለም፣
አማራ ተነሳ ኦሮሙማን ግጠም
በሂወትህ ቆርጠህ ሞት ሽረት ተፋለም፡፡
ደም በደም ካልጠራ ስለሚሆን መርገም
ባፈሰሰው ደም ልክ አፍስስ የኦነግ ደም
በደንብ አርገህ ቅጣው እንዳያስብ መድገም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለሃያ ሁለት ማዞሪያ ሰማእታት - አሁንገና ዓለማየሁ

መስፍን አረጋ

[email protected]

3 Comments

  1. ፕሮፌሰር መስፍን ጉዳዩ መች እንዲህ ሆነ የምን መግጠም አመጣህብን እንዲገጥመን በጀት በሳምንት ፫ መቶ ሚሊዮን ብርና ጦርነቱን በደምብ በመገናኛ እንዲያሳልጡት የቴሌፎንና የኢንፍራ ስትራቸር ገዥው ፓርቲ ለምኖ ሊጠግንላቸው ወደ ስራ ተገብቷል አዲሲቷ ኢትዮጵያ እንዲህ ነች። እነሱ ያወደሙትን የአማራ ንብረት የፈጁትን አማራ ማን ይጠይቅ በሰሜን የታረደው የኢትዮጵያ መከላከያ ፭ መቶ አመት የሞላው ያህል ተረስቷል። አገኘሁ ተሻገርም ይህንን ነገር ባላሳልጥ ሽጉጤን ጠጥቼ እሞታለሁ ብሏል አረቄ ጠጥቶ ይሞት እንደሁ እንጅ ለወገን ክብር እንደ ማይ ሞት ጥርጥር ባይኖረንም። ለማንኛውም ክልሉ ምን እስኪሆን እንደሚጠብቅ ግራ የገባ ነገር ሁኗል።

  2. ኢትዮጵያ በጎሳ የተካለለችና ጎሳዎች እስከ መገንጠል መብት የተሰጣቸው ህገ አራዊት ነው፡፡ ይህ ከሆነ ዘንዳ ስለ ወልቃይት የአብይ መንግስት ለአማራ ለመደራደር የምን የህግ አግባብ ይኖረዋል? ምን እንደሚያስብ ምን እንደሚደራደር ለፋኖ፤ለአማራ ክልል፤ለሱማሌ ክልል፤ለጉራጌ ክልል፤ለደቡብ ክልል ሳያሳውቅ በጠላትነት የሚያየው የኦሮሙማ መንግስት ድርድር መጥራቱ አግባብ አይመስልም፡፡

  3. አማራ ያለው አማራጭአንድ ብቻ ነው፡፡ በፋኖ ዙሪያ ከአሁኑ ይበልጥ በንቃትና በስፋት በሚሊዮኖች መደራጀት ከላይ እስከታች መደራጀት፣ ከሁሉም ይቀድማል፡፡ ከዚያው በተጓዳኝ በየነጥብ ጣቢያው ያሉትን የአብይ አህመድ ምስለኔወች ለመቀጣጫ በሚሆን መልኩ እያነቁ ማጥፋት፣ ማስወገድ፡፡ አማራ የለመደውን “ነፍጡን አንስቶ አካባቢውን እየጠበቀ ራሱን ከወያኔና ከኦሮሙማ መከላከል ብሎም ማሸነፍና ሌሎች ወንድም እኢትዮጵያዊያን (በአንዲነትና እኩልነት) የሚያምኑ ጋር ከጎጠኞችና የውጭ ጠላቶች (ሩቅም ቅርብም) አገሩን ማዳን ነው፡፡
    እርምጃው ከሰፈር ጀምሮ “”ማጽዳትን”” ኢላማ ያደረገ ቆራጥ እርምጃ መሆን ግድ ይለዋል፡፡
    ከዚያ በኋላ ሌላው ሌላው ገብስ ነው፡፤ ለአማራው ብናኞች ናቸው፡፡ አስቀድሞ ከውስጡ ሆዳሞቹን ማስወገድ ቅድሚያ ሊሰተው ይገባል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.