ግልጽ ደብዳቤ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶር አቢይ አህመድ –  ተፈራ መኮንን (ዶር)

ግልጽ ደብዳቤ                                                                                    Abiy 90   06-02-2022

ይህችን ማስታወሻ ዛሬ ለዕርሶዎ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ዋናው ምክንያት ሰሞኑን በህግ ማስከበር ስም ሺዎችን በግፍ ማሰር ፤ መሰወር ፤ እንዲሁም የህግ ታሳሪዎችን በአደባባይ ማሰደብደብ የአገዛዞ አይነተኛ መገለጫ እየሆነ በመምጣቱ ድርጊትዎ አገዛዞን የማያጸና በህግ ፊት ተጠያቂነት ያለው መሆኑን ለመጠቆም ነው።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር- በርሶው አገዛዝ በብዙ መቶ ሺህ በላይ ዜጎች ባላአስፈላጊ  የርስበርስ ጦርነት ውድ ሀይወታቸውን እንዲያጡ ሆነዋል።  አቅፈው ደግፈው በያዙት የዘር ፖለቲካ ብዙ ሚሊዮኖች  ከቤት ነብረታቸው ተፈናቅለው  ተመጽዋች ሆነዋል። በአገዛዞ ሀገራችን በተፈናቀሉ ዜጎች (IDP) ቁጥር  የመጀመርይ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በርካታ ጋዜጠኞችን፤ማህበሪያዊ አንቂዎችን፤ ከህጻን እስክ ሰማንያ አመት ሽማግሌ ሳይቀር አፎኖ መሰወር ያገዛዞ የዘወትር ስራም ሆናል።

የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስቴር – በርሶው አገዛዝ ሀገር አዝናለች። ልጆችዋ ተሳዳጅ፤ ተቅበዝባዥ ሆነዋል ። የኑሮ ውድነት ያጎበጠው ህዝብ የአገዛዞን አፈና መሸከም ተስኖታል። እርሶ ግን የአፈር ማዳበሪያ ለሚጠብቀው  የሀገሮ ገበሬ እሳት የሚተፋ ድሮን ና አልሞ ተኮሽ በመላክ ህዝቦትን በማሸበር ስራ ለይ ተጥምደዋል። አገዛዞ ዛላቂ የልማት ፕሮጀክቶችን ከመገንባት፤ ሽቅብ ብቻ ለሚነጉደው የኑሮ ውድነት ሀገራዊ የአጭርና የረዥም ግዜ  መፍትሄ ከማፈላልግ ይልቅ የተከሉት አባባ መጥፋት፤ የከተማዋ ህንጻዎች ቀለማት መዥጎርጎር  እርስዎ የመጡበት ጎሳ “የዘር መዝመር” በከተማዋ ት/ቤቶች አለመዘመር  አብዝቶ ሲያስጨንቆት አንዳንዴም ሲያናደዶት ይስተዋላል። በአጠቃላይ በእርሶዎ አገዛዝ ሀገራችን ሰላሞን ያጣች  ተስፋ ቢስና ለመበታተን አንድ ሀሙስ የቀራት ሀገር አድርገዋታል።

ስለዚህ ክቡር ጠቅልይ ሚኒስቲር- በቆዩበት የስልጣን ዘመንዎ ዘረኘነትን ፤ተረኝነትን ና ጥላቻን እንጂ ሰላምና ፍቅርን በምድሪቱ ላይ አያሰፈኑ አይደለም። ይህችን ታላቅ ሀገር የመምራት ችሎታውም ሆነ ቅንንነቱ ያልታየቦት በመሆኑ ስልጣኖን ለግዚያዊ የሽግግር መንግስት በማስረከብ ሀገሮትን ከመበታተን፤ ህዝቦትንም ከእርስበርስ ግጭት በማውጣት ያሳዘኑትን ህዝብ ውለታ አንዲውሉለት ስል በትህትና እጠይቆታለሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ‹‹በትግራይ ግጭት የተካሄደው የምርመራ ሪፖርት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት አግኝቷል›› – ዶክተር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር

ከሰላምታ ጋር

ተፈራ መኮንን (ዶር)

3 Comments

  1. That is the right and courageous or patriotic way of telling the truth or calling a spade and spade and making a very clear and straightforward solution (means) if the country should be saved from a very disastrous end of falling apart!!!
    Great and quite rational message!!!!

  2. አለቃ ደግ ብለሀል የጎደለ ነገር ቢኖር ንጹሀንን፣ማሰር፣ማፈናቀል እረፍት መንሳት ብቻ ሳይሆን ወንጀለኛን ማደፋፈር፣ነጻ ማውጣት፣ከእስር መልቀቅን ይጨምራል። በቅርቡ የአዲስ አበባ ህዝብ ኦሮሞን ይጠላል ብሎ አንድ መሪ ሲናገር በሮቦት መልክ የተዋቀረውን የሽመልስ አብዲሳን፣የአብይ አህመድንና የጁዋር መሀመድን ቄሮ የደም መስዋእትህን አቅርብ ማለት ነው።

  3. What Lidetu Ayalew said about Abiy (PP), that Abiy (PP) can only take the country from one crisis to another even deeper crisis, is being proven.
    Yes, enough of this bloodshed, cruelty and distraction. Time for Abiy to exit, for the constitution to be suspended and for a transitional system to take over government power. Abiy does not have the will or ability to defeat the terrorist OLF and TPLF. He, in fact, is conducting state-sponsored terrorism right now. He has shown that he lacks vision and any concrete socio-economic plans that can positively transform the country.
    Yes, PM, It is time to gracefully exit. Sure there are 81 ethnic groups and several religions availing you with more than plenty fuel for instigating conflict and orchestrating genocide just to stay in power. But the end is going to be ugly. Very ugly, for both yourself and the country. So, take the doctor’s advice and execute a nice exit.

Leave a Reply

Your email address will not be published.